በድሬደዋ ከተማ ዛሬ ጠዋት ላይ በጣለው ከባድ ዝናብ ሳቢያ የአንድ ድርጅት አጥር ግንብ ፈርሶ በሶስት መኖሪያ ቤቶች ላይ በመውደቁ የዘጠኝ ሰዎች ህይወት አለፈ::
–
በአደጋው ህይወታቸው ካለፈው ውስጥም አንድ የሶስት ወር ጨቅላ እና እንዲሁም የሁለትና የአምስት አመት ህፃንናት ይገኙበታል::
–
ዛሬ ከረፋዱ ሁለት ሰአት ጀምሮ ባለማቋረጥ ከአራት ሰአታት በላይ በጣለው ከባድ ዝናብ ሳቢያ በድሬደዋ ከተማ ቀበሌ 03 ሸመንተሪያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ከቀኑ ስድስት ሰአት ገደማ የባሻንፈር ትሬዲንግ ድርጅት እስከ ሀምሳ ሜትር የሚጠጋ የአጥር ግንብ በግንቡ ዙሪያ ባሉ ሶስት የተለያዩ መኖሪያ ቤቶች ላይ ፈርሶ በመውደቁ በቤቱ ውስጥ የነበሩ ዘጠኝ ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ማለፉን የኮሚሽኑ የህ/ግንኙነት ዋና ክፍል ሃላፊ ም/ኢ/ር ባንታለም ግርማ ገልፀዋል::
–
ሃላፊው አያይዘውም ከሟቾች ውስጥ አንዲት አራስ እናት ከሶስት ወር አራስ ጨቅላ ልጇን ባለቤቷ ጋር ህይወት ሲያልፍ አንድ የሁለት አመት እና አንድ አምስት አመት ህፃናን በአደጋው ህይወታቸው አልፏል ብለዋል::
–
የድሬደዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን በአደጋው በደረሰው ህልፈት ህይወት የተሰማውን ልባዊ ሀዘን ገልፀው በድሬደዋ ከተማ ከወትሮው በተለየ መልኩ ዝናብ በከፍተኛ ሁኔታ እየጣለና በቀጣይ ቀናትም ይሄው ተጠናክሮ የሚቀጥልና የጎርፍ አደጋም ሊያስከትል የሚችል ስለመሆኑ ቤሄራዊ ሜትሮሎጂ የገለፀ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ መላው ህብረተሰብ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግም ም/ኢ/ር ባንታለም ግርማ ጨምረው አሳስበዋል::
–
ምንጭ፦ የድሬደዋ አስተዳደር ፓሊስ ኮሚሽን
–