የአፋር እና የሶማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስታት በርዕሳነ መስተዳድሮቻቸው የተመራ የከፍተኛ አመራሮች ቡድን በቅርቡ በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ ቀበሌዎች የተፈጠሩ ግጭቶችን በሰላም ለመፍታት ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡
–
ርዕሳነ መስተዳድሮቻቸው በሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ሰብሳቢነት ነው ዛሬ ስምምነት ላይ የደረሱት፡፡
–
በሰላም ሚኒስቴር የሁለቱ ክልሎች ከፍተኛ አመራሮችና የፌደራል መንግስት የጸጥታ አካላት በተገኙበት በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ ቀበሌያት የተከሰቱ ግጭቶችን በአፋጣኝ ለማስቆምና በቀጣይ ችግሮችን ለመፍታት መስማማታቸውንም ከሰላም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
–