የሕዳሴው ግድብ የኪንሻሳው ድርድር ሲቋረጥ በሁሉም ተደራዳሪዎች ዘንድ የንዴትና የብስጭት ስሜት ይታይ ነበር

የአፍሪካ ኅብረት የወቅቱ ሊቀመንበር በሆኑት የኮንጎ ዴሞክራሲያዊት ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ፌሊክስ-አንቷን ሺሴኬዲ አደራዳሪነት ዋና ከተማዪቱ ኪንሻሳ ላይ ከትናንት በስተያ ተጀምሮ የነበረው የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ ድርድር ያለስኬት ተበትኗል።ድርድሩ ሲቋረጥ በሁሉም ተደራዳሪዎች ዘንድ የንዴትና የብስጭት ስሜት ይታይ እንደነበር ኪንሻሳ የምትገኘው ሪፖርተራችን አናስታሲ ቱዴሺ ትዝብቷን ዘግባለች።በሦስቱም ወገኖች የተንፀባረቀው የመወነጃጀል ስሜት መሆኑንም የሰጧቸው መግለጫዎች ያሳያሉ።በአባይ ውኃ ምክንያት በአካባቢው የግጭት ሥጋት ያየለ ሲሆን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ግን ወገኖቹ ልዩነቶችን በማቻቻልና በመተባበር መንፈስ መነጋገራቸውን እንዲቀጥሉ አሳስቧል። የድርድሩ ሁኔታ ኪንሻሳ ላይ ምን ይመስል እንደነበረና የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ የሆኑት የውኃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ኃይል ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ ዛሬ አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ ላይ የተጠናቀሩትን ዘገባዎች ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።