ዶክተር አረጋዊ በርሔ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሄራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ።
–
ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐብይ አህመድ ለህወሐት መስራችና የቀድሞ አመራር ለነበሩት አቶ አረጋዊ በርሔ (ዶ/ር) ይህንን ሹመት መስጠታቸውን ከጠቅላይ ሚኒስቴሩ ቢሮ ማህበራዊ ሚዲያ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።
–
ከዚህ ቀደም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሄራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤትን በዋና ዳይሬክተር ሲያገለግሉ የነበሩት ወይዘሮ ሮማን ገብረስላሴ ነበሩ።
–
ዶክተር አረጋዊ በርሄ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ትዴፓ) ሊቀ-መንበር መሆናቸው ይታወቃል።