- የፖለቲካ ፓርቲዎች ባልደራስ ያቀረበውን የአዲስ አበባን የራስ ገዝነት ጥያቄ እንደሚደግፉ ገለፁ።
- በባልደራስ ዋና ፅ/ቤት ዛሬ በተካሄደው የፓርቲዎች የጋራ ምክክር ላይ ነው ይህንን ያሉት።
–
ምን ምን ነጥቦች ተነሱ…..
–
ተሳታፊ ፓርቲዎች ሀሳባቸውን ሲገልፁ የአዲስ አበባ ጉዳይ እጅግ ይመለከተናል አብሮ መስራት በጣም አስፈላጊ ነው ብለዋል።
–
ከአዲስ አበባ ራስ ገዝ አስተዳደር ጥያቄው በተጨማሪ …በተረኛው መንግስት አስተዳደራዊ በደል ላይ በጋራ ልንሰራ ይገባል። በተጨማሪም አገራዊ መግባባት እንዲመጣና ሕገ_ መንግስቱ እንዲለወጥ አብረን መስራት አለብን የሚሉ ሀሳቦች ተንሸራሽረዋል።
–
.ባልደራስ ጠንካራ አገራዊ አጀንዳዎችን እያመጣ ከፊት ሆኖ ለሚያደርገው ትግል እውቅና እንሰጣለን። የባልደራስ ፕሬዝዳንት እስክንድር ነጋ ከጅምሩ ያደርግ የነበረውን ትግል አደንቃለሁ። ብለው የተናገሩ የፖለቲካ አመራርም ነበሩ።
–
የአዲስ አበባ መዋቅራዊ ችግር ይፈታል ብለን የምናምነው ሕገ_መንገስቱ ሲቀየር ነው ብለው እንደሚያምኑ ፓርቲዎቹ ደጋግመው ገልፀዋል። በስተመጨረሻ ፓርቲዎቹ ውይይቱ ሁሉን አካታች ውይይት መሆን እንደሚኖርበት የተወያየዩ ሲሆን ለመነሻ ዛሬ የተወያዮት ፓርቲዎች ባልደራስን ጨምሮ 6 ፓርቲዎች ነበሩ።
–
በዛሬው ቀን የተሰበሰቡት ፓርቲዎች ሰብሰባውን ሲደመድሙ በሶስት ሳምንት ውስጥ እንደገና ተገናኝቶ ለመወያየት ወስነዋል።