የጽንፈኛ ቄሮ መሪ ጦርነት አውጇል – እንግዲህ ሕዝብ ሆይ ራስህን ተከላከል #ግርማካሳ

የጽንፈኛው ቄሮ መሪ ጃዋር መሐመድ ለኦሮሞ ክልል መንግስት ሌላ መመሪያ አስተላልፏል። በፌስ ቡክ ገጹ ላይ የሚከተለውን ነበር የለጠፈው፡

“Dhaabbileen Miti-Mootummaa ( NGO) Oromiyaa keessa jiran irra jireessi isaanii Afaan Oromoon hin hojjatan. Kaayyoon isaanii ummata naannichaa tajaajiluu erga tahee afaan naanichaan dubbachuu qabu. Afaan Oromoon hojjachaa dhalattoota naannoo sanii hiree hojii dhoowwachaa itti fufuu hin qaban. Oromiyaa kleessa turuu yoo barbaadan afaan Oromoon hojjachuu; san didnaan dhoortoo isaanii qabatanii haa bayan.”

አንድ ላቲን የሚያነብ ፣ ግን በላቲን ኦሮምኛ በአገራችን ፊደል እንዲጻፍ እየሰራ ያለ የኦሮሞ ልጅ ወዳጄ፣ ብርሃኑ ገመቹ ትርጉሙን እንደሚከተለው አቀበለኝ።

“በኦሮምያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ በብዛት በኦሮምኛ አይሰሩም። ዓላማቸው ህዝቡን ማገልገል ከሆነ የክልሉን ቋንቋ መናገር አለባቸው። በኦሮምኛ ባለመስራት የክልሉን ተወላጅ ስራ መንፈግ የለባቸውም። በኦሮምያ በስራ ለመቀጠል የሚፈልጉ ከሆን በኦሮምኛ መስራት አለባቸው። አለበለዚያ ግን በአስቸኳይ ተጠራርገው መውጣት አለባቸው”

ከዚህ በፊትም ጃዋር “Ethiopians Out of Oromia” እያለ የጽንፈኛ አክራሪዎችን ሰልፍ ሲመራ እንደነበረ ሁላችንም የምናውቀው ነው። ያኔ ጃዋር ብዙ ደጋፊ አልነበረውም። አሁን ግን በመቶ ሺሆች የሚቆጠሩ፣ ገደል ግቡ ቢላቸው ገደል የሚገቡ ጭፍን ደጋፊዎች አሉት። በተለይም በምእራብ አርሲ ፣ በባሌና በሃረርጌ ዞኖች።
በተጨማሪም በኦህዴድ/ኦዴፓ መዋቅር ውስጥም ከነ ዶ/ር አብይ በበለጠ በጣም ተጽኖ ፈጣሪ ነው። በአብዛኛው ነዋሪ በማይደገፍበት ቦታ ደግም፣ ያሰማራቸው የማፊያ ቄሮ ቡድኖች አሉ። በጣም ጥቂቶች። ለምሳሌ ለገጣፎ አብዛኛው ነዋሪ ኦሮሞዉን ሳይቀር በሰላም በፍቅር የሚኖር ነው። ግን እዚያ ፋይናንስ የተደረጉ ቄሮዎች፣ በአካባቢው የኦህደድ ሃላፊዎች እየተደገፉ፣ የነጃዋርንና እነከጃዋር ጋር የሚሰሩ ኦህዴዶችን ቁሻሻ ስራ እየሰሩ ነው። በመሆኑም ይሄን የጃዋር ንግግሩን ችላ ብሎ መቀመጥ በራስ ላይ መፍረድ ነው።

ይህ የጃዋር ንግግር፣ በኦሮሞ ክልል በሚኖሩ፣ ኦሮምኛ በማይናገሩ ዜጎቻችን ላይ ጦርነት ማወጅ ነው። ይህ ሰው በሲዳማ ዞን፣ ታናሽ ወንድሞቹ ኢጂቶዎች በጉልበት የፈለጉትን እንዲያደርጉ ቀስቅሶ፣ ኢጂቶዎችም የልብ ልብ ተሰምቷቸው አካባቢዉን እንዳሸበሩ፣ ከፍተኛ የዘር ተኮር ግድያዎች እንደፈጸሙ፣ ብዙ ንብረቶች እንዳቃጠሉ የሚታወስ ነው። ያኔ ጃዋር ምንም አልተባለም። አሁን ደግሞ በኦሮሞ ክልል፣ በሌሎች ማህበረሰባት በይፋ ዘመቻ አዉጇል።

ከሁለት ወራት በፊት ኢትዮጵያ የነበርኩ ጊዜ ሰበታ፣ ሳንሱሲ፣ ለገጣፎ፣ አዳማ የመሳሰሉ በሸዋ ያሉ በርካታ አካባቢዎችን አይቻለሁ። በአዳማ እንዳለ ሰው አማርኛ ተናጋሪ ነው። ማስታወቂያዎች በላቲንም ይጻፋሉ፣ ያው በግዳጅ። ከዚያ በተረፈ ግን ሆቴል ቤቶች ፣ መጽናኛ ቦታዎች፣ ሱቆች፣ ምግብ ቤቶች..ሁሉም የሚሰሩትና የሚናገሩት በአማርኛ ነው።
አዳማ አዲስ አበባ ናት። ሰበታም እንደዚሁ ነው።መንደር ሱቆች ሁሉ ስገባ ነበር። በተለይም በምስራቅና ሰሜን ሸዋ ዞኖች ባሉ ከተሞች፣ በአዳማ፣ በቢሾፍቱ፣ በሞጆ፣ በዱከም፣ በቡራዩ፣ በጣፎ፣ በአለምገና፣በመተሃራ፣ በዝዋይ፣ በአርሲ ነገሌ … ኦሮምኛ የማይናገሩ ከሰባ፣ ሰማኒያ በመቶ በላይ ናቸው። በሻሸመኔ፣ ጂማ፣ አሰላ በመሳሰሉትም እንደዚሁ።

ከተሞቹን ትተን በወረዳ ደረጃ እንኳን ብንመለከት፣ ከአስራ ሶስት አመታት በፊት በተደረገው የሕዝብ ቆጠራ ውጤት መሰረት፣ በአዳማና አዳም ዙሪያ ወረዳ ከ65% በላይ፣ በደራ ከ53% በላይ፣ በፈንታሌ ከ61% በላይ ፣ በግራር ጃርሶ ከ50% በላይ፣ በሎሜ ከ43% በላይ፣ በቆቂር ከ41% በላይ፣ በአዳ ጩሉቃ ከ37% ..የሚሆኑት ኦሮምኛ ተናጋሪ አይደሉም። አሁንም ደግሞ ቆጠራ ቢደረግ፣ ቁጥሩ የበለጠ ነው የሚጨምረው። ያለ ንም ጥርጥር በሰሜን ሸዋ፣ በደቡብ ምእራብ ሸዋና በምስራቅ ሸዋ፣ ኦሮምኛ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ከሆኑት፣ ኦሮምኛ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ያልሆኑ ነው የሚበልጡት።

እንግዲህ ሜዳ ላይ ያለው እውነታ እንደዚያ ሆኖ ጥቂት ዘረኞች ፍላጎታቸው በሃይል፣ በማስፈራራት ለመጫን መሞከራቸው የተኛውን ዝሆን እንደመቀስቀስ ነው። ዝም ሲባሉ፣ ሰው ሲታገሳቸው የፈራቸው እየመሰላቸው ነው።

እነ ጃዋርን ተከትሎ የሺመልስ አብዲሳ መንግስት አፓርታይዳዊ፣ ሕግ ወጥ እንቅስቃሴዎች ለመጀመር ሊዳዳው ይችላል። ያንን መታገል ብቻ ሳይሆን ታግሎ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማሸነፍ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው የሚሆነው።

ደግሜ እላለሁ ህዝቡ ነቅቶ፣ በአስቸኳይ ካልተደራጀና ካልተንቀሳቀሰ ፣ ዝም ብሎ ከተቀመጠ ፣ የሚያድነው፣ ለርሱ የሚቆምለት ማንም አይኖርም። ሰዎቹ ጨካኝና ዘረኛ ናቸው። ሰው ዘቅዝቀው ከመስቀል ወደ ኋላ አይሉም። 1.4 ሚሊዮን ጌዶዎችን በጭካኔ ኦሮሞ አይደላችሁም ብለው ያፈናቀሉ ናቸው። በቡራዩ ያደረጉትን ሁላችንም እናስታወሳለን። በለገጣፎም እንደዚሁ። አሁን ጃዋር በአደባባይ የሰጣቸውን መመሪያ አያደረጉም ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው።