Blog Archives

የእናቶች ዋይታ! በመተማ ሆስፒታል! ቤተሰቦቻቸው ቁስለኞችን ገብተው መጠየቅ እንደማይችሉ ተነግሯቸዋል።

የሱዳን ሰራዊት ከትህነግ/ህወሓት ጋር በመተባበር በአማራ ገበሬዎች ላይ በፈፀመው ወረራ የቆሰሉት ገበሬዎች ገንዳውሃ ከተማ መተማ የመጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል ገብተዋል። ሆኖም ቤተሰቦቻቸው ቁስለኞችን ገብተው መጠየቅ እንደማይችሉ ተነግሯቸዋል። የእናቶች ዋይታ! በመተማ ሆስፒታል! የደርግን መውደቅ ካስደስታቸው መከካል እናቶች ይቀድማሉ። “ዘመቻ የለም፣ ገፈፋ የለም፣ ጦርነት የለም” ይሉ ነበር። ልጆቻቸው ወደ ጦር ሜዳ በግድ ዝመቱ የተባሉባቸው እናቶች። ይህን ካሉ ግን ቆይተዋል። ዛሬም ቢሆን ጦርነት አለ። ዛሬም ከደርግ የባሰ ጭራቅ ሀይል አለ። ዳር ድንበሩን ለጠላት አሳልፎ የሚሰጥ። ዳር ደንበሩን አሳልፎ ከሰጠው ጠላት ጋር ሆኖ ንፁሃንን በከባድ መሳርያ የሚጨርስ ጭራቅ ሀይል አለ። ከደርግ የባሰ! ይህ የምታዩት ፎቶ ዛሬ የተነሳ ነው። ገንዳውሃ ከተማ መተማ ሆስፒታል ፊት ለፊት ነው። ትህነግ የሱዳን ጦርን መርቶ ቤተሰባቸውን በከባድ መሳርያ ያስመታባቸው እናት ሲያለቅሱ የሚያሳይ ነው። አንድ አባት ሊያፅናኑዋቸው ሲጥሩ ያሳያል። ትህነግ የከፈለው የሱዳን ጦር ደንበር ጥሶ ሲመጣ የኢትዮጵያ የሚጠብቅ ጦር አልነበረም። የሱዳኑንም፣ የኢትዮጵያ ነው የሚባለውንም የሚመሩት ትህነጎች ናቸው። እናቶች ደግሞ ዋይታቸውን ለማንም ማሰማት አይችሉም። ወራሪውም አስወራሪውም ጠላት አድርጎ ፈርጇቸዋል። ደርግ እንኳን ወደቀ ያሉ እናቶች ከደርግ የባሰ ጭራቅ ጥሎባቸዋል። ዛሬም ዋይታቸው ቀጥሏል! የሱዳን ጦር በአማራ ገበሬዎች ላይ የከፈተው ጦርነት የጀመረው ሰኔ 25/2010 ዓም ነው የሚባለው ስህተት ነው። ሰሚ ጆሮ አጥቶ ነው እንጅ ወረራው በአዲስ መልክ ወረራው ከጀመረ ከ25 ቀን በላይ ሆኖታል። ማስተካከያ የሚያስፈልገው ባለፉት ሶስት ሳምንታትም በርካታ ገበሬዎች ስለተገደሉ፣ ስለቆሰሉና ስለጠፉ ነው! ይህ ሁሉ
Tagged with: , , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሕወሓት በአሶሳ ሲነቃበት በሱዳን በኩል በአማራ ገበሬዎች ላይ የውክልና ጦርነት ጀምሯለ 

በሱዳን ጦር ከባድ መሳርያ ተኩስ ተከፍቶባቸው የቆሰሉት አማራ ገበሬዎች ገንዳውሃ የሚገኘው መተማ ሆስፒታል ገብተዋል።እስካሁን በሁለት አንቡላንስ የመጡ ቁስለኞች ወደ ሆስፒታል ገብተዋል ተብሏል። ሕወሓት በአጋዚ አልበቃውም! በአልበሽር ጦር የአማራ ገበሬዎችን እያስጨፈጨፈ ነው። በአሶሳ ሲነቃበት በሱዳን በኩል የውክልና ጦርነት ጀምሯል። በአማራ ገበሬዎች ላይ! የአማራ ገበሬዎችን እያስጨፈጨፈ ያለው ትህነግ ነው ከሱዳን ሰራዊት ጋር ሆኖ የአማራ ገበሬዎችን እየጨፈጨፈ ያለው ህወሓት መሆኑን ቁስለኞቹ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ የመጣው የሱዳን ጦር ጋር ገጥመው የቆሰሉት በግልፅ ተናግረዋል። የገጠማቸው ሕወሓት ነው። እነሱ የሕዝብ ስም ጠርተው ነበር የተናገሩት። ላኪው ትህነግ/ህወሓት ነው በሚል ነው። ጦርነቱን መርቶ የአማራ ገበሬዎችን እየጨፈጨፈ ያለው ትህነግ/ህወሓት ነው! ከቁስለኞቹ ባሻገር የልዩ ሀይሉ ሃላፊ ለገንዳውሃ ኃላፊዎች ጦርነቱን እየመራው የሚገኘው ሕወሓት ነው ብሏል። ገንዳውሃ ሆስፒታል 7 ቁስለኞች ገብተዋል አምስቱ ገበሬዎች ሲሆኑ ሁለቱ በሱዳን መከላከያ እና በገበሬዎቹ መካከል “ሽምግልና” አርፍዶ ዘግይቶ የገባው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ናቸው። ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ገበሬዎች እንዳሉ ታውቋል። ሁለቱ የመከላከያ ሰራዊቱ አባላት ወደ ጎንደር ሆስፒታል እንዲላኩ “ሪፈር” እንደተባለላቸው ተገልፆአል። ከደደሎ ወደ ገንዳውሃ የሚመጡ ተጨማሪ ቁስለኞች እንዳሉ ተገልፆአል። ብዙ ቁስለኞች ሸኸዲ ሆስፒታል ገብተዋል! ከቆሰሉት ገበሬዎች መካከል አበጀ አንዱ ነው። አበጀ የ37 አመት እድሜ ያለው ሲሆን ቋራ ወረዳ ቁጥር አራት ነፍስ ገበያ አካባቢ ነዋሪ ነው። ከሱዳን ሰራዊት በተተኮሰ ከባድ መሳርያ ብዙ አማራ ገበሬዎች ተገድለዋል። ቆስለዋል። የሱዳን ሰራዊት የሁለት ገበሬዎችን አስከሬን ወደኋላ አሽሽቷል። የጠፉ ገበሬዎች እንዳሉም ታውቋል። የአማራ
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በሱዳን ጦር እና በጎንደር ገበሬዎች መካከል ጦርነቱ ተፋፍሟል።

“መንግስት” አልባው ሕዝብ ከሱዳን ጋር ሊገጥም ነው (ጌታቸው ሽፈራው) ባለፉት ሳምንታት የሱዳን ጦር በአማራ ገበሬዎች ላይ ጦርነት ከፍቷል። ትናንት ሰኔ 25/2010 ዓም ገበሬዎች ከሱዳን ሰራዊት ጋር ውሏቸውን ሲታኮሱ ውለዋል። የሱዳን ጦር አፈና የፈፀመባቸውን 70 ያህል ገበሬዎች ነፃ ለማውጣት በተደረገ ጦርነት ብዙ ገበሬዎች ተገድለዋል። ቆስለዋል። በጦርነቱ የተሰውት ላቀው ሰለሞንና ገብሬ አውለው አስከሬን ወደ ቤተሰብ ሲላክ ከአምስት በላይ ገበሬዎች ቁስለኛ ሆነዋል። የአቶ ለቀው ሰለሞን እና የገብሬ አውለው መገደል ከተሰማ በኋላ የመተማ፣ የሸህዲና የአርማጭሆ ህዝብ ከሱዳን ጦር ጋር ለመግጠውም መወሰኑ ተሰምቷል። በዛሬው ዕለት የመተማ ነዋሪዎች በአይሱዚ መኪና ጦርነት ወደተነሳበት ደለሎ እየሄዱ መሆኑን ገልፀውልኛል። የ”ኢትዮጵያ መከላከያ” ሰሞኑን ወደ ደንበር ቢጠጋም የኢትዮጵያ ገበሬዎች በሱዳን ጦር ሲዘመትባቸው ዳር ዳር ተመልካች ሆኗል። ዛሬ ሰኔ 26/2010 ዓም የአማራ ልዩ ሀይል ከሕዝቡ ጋር ወደ ደለሎ መሄዱም ተጠቁሟል። የአማራ ገበሬዎች የሀገር ዳር ድንበር ጥሶ የመጣው ጦር ጋር ፊት ለፊት ገጥመው የመከላከያ ሰራዊቱ ከድንበር ርቆ ከርሟል። መንግስት ነኝ የሚል አካልም ሆነ ስለ ሀገር ዳር ድንበር ያገባኛል የሚል አካል ስለ ገበሬዎቹ ሞት ጆሮ አልሰጡም። የአማራ ገበሬ የድጋፍ ሰልፍ ሲወጣ ኢትዮጵያዊ ይባል፣ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በቃታ ብረት እየጠበቀ ሲሰዋ ግን ሞቱን የሚያወራ የለም። በወራሪ ጦር ሲገደል አማራ ነው!
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News