Blog Archives

በጎንደር ድንበር ጥሶ የሚገባው በሱዳን ጦር ብዙ ጥፋት እየደረሰ ነው።

የሱዳን ወረራ ጉዳይ! ትናንት ከቀኑ 9:30 ድንበር ጥሶ ገብቶ የነበረው የሱዳን ሰራዊት ከምሽቱ 1 ሰዓት አካባቢ ተመልሷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት፣ የሱዳን ጦር በገበሬው ላይ ሲተኩስ ባይደርስም ከሁለት ሰዓት በኋላ ወደ አካባቢው አቅንቶ ነበር። የአማራ ክልል ሚሊሻ ቀድሞ ወደ ቦታው መድረሱም ታውቋል። መከላከያ ሰራዊት እየደረሰ ያለው የሱዳን ጦር ድንበር ጥሶ፣ ገበሬዎችና ንብረታቸው ላይ ጉዳት ከደረሰ በኋላ ነው። ትናንት የአንድ ገበሬ ካምፕ በሱዳን ጦር ተቃጥሏል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ሉአላዊነትን ባለማስከበሩ በሱዳን ጦር ብዙ ጥፋት እየደረሰ ነው። ለጥፋቱም ተጠያቂ የሚሆን አካል አልተገኘም። የዶክተር አብይ መንግስት በአማራ ገበሬዎች ላይ ለሚደርሰው ወረራና ስቃይ ቁብ አልሰጠም! በየጊዜው ወረራ ይፈፀማል። ሉአላዊነትና የዜጎችን ደሕንነት የማስጠበቅ ግዴታ ያለበት የፌደራልም ሆነ የክልል መንግስት ግዴታውን እየተወጣ አይደለም።
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በመተማ የተደረገው ህዝባዊ ስብሰባ የአቋም መግለጫ በማውጣትና ለመንግስት የሁለት ቀን የጊዜ ገደብ በመስጠት ተጠናቀቀ

በመተማ ደለሎ ቁጥር አንድ ላይ ትናንት ሰኔ 29 ቀን 2010 ዓ•ም የተደረገው ህዝባዊ ስብሰባ አምስት የአቋም መግለጫዎችን በማውጣት እና ለመንግስት የሁለት ቀን የጊዜ ገደብ በመስጠት መጠናቀቁ ተሰማ ከመተማ፣ከገንዳ ውሀ፣መሽሀ፣ላስታ፣ሽመለ ጋራ፣ከምዕራብ አርማጭሆ አብርሀ ጅራ እና ከሌሎችም አካባቢዎች ጥሪ የተደረገለት በአጠቃላይ እስከ 2000 የሚደርስ ህዝብ በስብሰባው ላይ መሳተፉ ተነግሯል። በተለይ ሰሞኑን ለዳር ድንበራችን መከበር የተሰውትን አቶ ገብሬ አውለውንና ላቀው ሰሎሞንን በከባድ የተኩስ እሩምታ፣በጀግና ፍከራና ቀረርቶ ታጅቦ የቀብር ስነ ስርዓታቸውን የፈፀመው የመተማና ገንዳ ውሀ ህዝብ በከፍተኛ ቁጥር፣ሞራልና ተነሳሽነት በህዝባዊ ስብሰባው ላይ ተሳትፏል ተብሏል። ስብሰባው በህዝብ የተመራ ቢሆንም የምዕራብ ጎንደር ዞን የአስተዳደርና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ ኮማንደር ጌትነት፣የዞኑ የድርጅት ጉዳይ ጽ/ቤት ሀላፊና መሬታችንን አነ አባይ ፀሀየ አሳልፈው ሲሰጡ በወቅቱ የመተማ አስተዳደርና ፀጥታ ሀላፊ የነበረውና በአሁኑ ስዓት የዞኑ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ ሆኖ የተሾመው አቶ አብነት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው በሽብር ወንጀል ታስረው የተፈቱት እነ ሀይሌ ማሞና ነጋ ባንቲሁን በስብሰባው ላይ መገኘታቸው ታውቋል። የመከላከያ ሀላፊው ኮሎኔል ሻምበል በስፍረው ባይገኝም በስብሰባው ላይ ተደውሎለት ሀሳብ እንዲሰጥበት መደረጉ ተገልጧል። የስብሰባው አጀንዳም የታጠቁ የሱዳን ወታደሮችን የትንኮሳ ጥቃት በመመከት ብሎም ዳር ድንበራችንን ቢያንስ እስከ ጓንግ ለማስከበር በጋንታ እና በቲም የመደራጀት አስፈላጊነትን የተመለከተ ነበር ተብሏል። በስብሰባው ላይም በደለሎ ቁጥር 4 ከሱዳን ወታደሮች በቅርብ ርቀት ጎድቦ ያለው መከላከያ ሰራዊት ዳር ድንበሩን የማስከበር ታሪካዊ ሀላፊነቱን እንዲወጣ ተገቢ የሆነ ትዕዛዝ እንዲሰጠውና ጓንግ ወዲህ ማዶ ሰፍሮ ያለን የሱዳን
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በሱዳን ጦር እና በጎንደር ገበሬዎች መካከል ጦርነቱ ተፋፍሟል።

“መንግስት” አልባው ሕዝብ ከሱዳን ጋር ሊገጥም ነው (ጌታቸው ሽፈራው) ባለፉት ሳምንታት የሱዳን ጦር በአማራ ገበሬዎች ላይ ጦርነት ከፍቷል። ትናንት ሰኔ 25/2010 ዓም ገበሬዎች ከሱዳን ሰራዊት ጋር ውሏቸውን ሲታኮሱ ውለዋል። የሱዳን ጦር አፈና የፈፀመባቸውን 70 ያህል ገበሬዎች ነፃ ለማውጣት በተደረገ ጦርነት ብዙ ገበሬዎች ተገድለዋል። ቆስለዋል። በጦርነቱ የተሰውት ላቀው ሰለሞንና ገብሬ አውለው አስከሬን ወደ ቤተሰብ ሲላክ ከአምስት በላይ ገበሬዎች ቁስለኛ ሆነዋል። የአቶ ለቀው ሰለሞን እና የገብሬ አውለው መገደል ከተሰማ በኋላ የመተማ፣ የሸህዲና የአርማጭሆ ህዝብ ከሱዳን ጦር ጋር ለመግጠውም መወሰኑ ተሰምቷል። በዛሬው ዕለት የመተማ ነዋሪዎች በአይሱዚ መኪና ጦርነት ወደተነሳበት ደለሎ እየሄዱ መሆኑን ገልፀውልኛል። የ”ኢትዮጵያ መከላከያ” ሰሞኑን ወደ ደንበር ቢጠጋም የኢትዮጵያ ገበሬዎች በሱዳን ጦር ሲዘመትባቸው ዳር ዳር ተመልካች ሆኗል። ዛሬ ሰኔ 26/2010 ዓም የአማራ ልዩ ሀይል ከሕዝቡ ጋር ወደ ደለሎ መሄዱም ተጠቁሟል። የአማራ ገበሬዎች የሀገር ዳር ድንበር ጥሶ የመጣው ጦር ጋር ፊት ለፊት ገጥመው የመከላከያ ሰራዊቱ ከድንበር ርቆ ከርሟል። መንግስት ነኝ የሚል አካልም ሆነ ስለ ሀገር ዳር ድንበር ያገባኛል የሚል አካል ስለ ገበሬዎቹ ሞት ጆሮ አልሰጡም። የአማራ ገበሬ የድጋፍ ሰልፍ ሲወጣ ኢትዮጵያዊ ይባል፣ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በቃታ ብረት እየጠበቀ ሲሰዋ ግን ሞቱን የሚያወራ የለም። በወራሪ ጦር ሲገደል አማራ ነው!
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News