ጄኔራል ባጫ ደበሌ በትግራይ ሲቪል ዜጎች ላይ ያነጣጠረ የአየር ጥቃት ይፈጸማል መባሉን አጣጥለው ነቅፈውታል፡፡

DW : የኢትዮጵያ መከላከያ ባሁን ወቅት እየሠራ ያለው በሰሜን ኢትዮጵያ መንግሥትን የሚዋጋው የህወሓት ኃይል እስካልጠፋ የተረጋጋ ሰላም ሊመጣ እንደማይችል አቋም ይዞ መሆኑን የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ግንባታ ሥራዎች ዋና አስተባባሪ ጄኔራል ባጫ ደበሌ ገለጹ፡፡ ጄኔራል ባጫ ከዶቼ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላት ያሏቸው፤ ከውስጥ የሚልኳቸው ብኖራቸውም እንኳ ኢትዮጵያን ማሸነፍ እንደማይችሉ እስኪረጋገጥ የሚያበቃ ጦርነት የለም ብለዋል፡፡

አሁን ላይ በሰሜን ኢትዮጵያ በተወሰኑ አከባቢዎች ካሉ አነስተኛ ግጭት ውጪ ከባድ የሚባል ጦርነት የለም ያሉት ጄኔራሉ፤ በትግራይ ሲቪል ዜጎች ላይ ያነጣጠረ የአየር ጥቃት ይፈጸማል መባሉን አጣጥለው ነቅፈውታል፡፡