መንግስት ከፋኖ አደረጃጀት ጋር ውይይት አደረኩ ያለው በራሱ መንገድ እንጂ በእኛ እውቅና የለውም። – የአማራ ህዝባዊ ኅይል/ፋኖ/

የአማራ ህዝባዊ ኅይል/ፋኖ/ መልስ ሰጠ
””””'””””””
የአማራ ክልል መንግስት ፋኖን ትጥቅ የማስፈታት ሃሳብ የሌለው መሆኑን የሚገልፅ ዜና በመንግስት ተቋማት የማህበራዊ ገፆች ተመልክተናል። ከዚህ ዜና ጋር በተያያዘ መንግስት ከፋኖ አደረጃጀት አባላት ጋር ውይይት አድርጌያለሁ በማለት ዜና አሰርቷል።
ዛሬ ጥር 06 ቀን 2014 ዓ.ም መንግስት ከተወሰኑ ፋኖወች ጋር ስብሰባ እንደሚያደረግ መረጃ ቢኖረንም እኛ በማናዉቀው እና የስብሰባው አዘጋጆች በሚያውቁት ምክንያት መንግስት የውይይት ጥሪውን ያደረገው መደበኛ ባልሆነ መንገድ ከመሆኑም ባሻገር ለአማራ ህዝባዊ ኃይል (ፋኖ) እና ከአደረጃጀታችን ጋር ለሚሰሩ በርካታ ፋኖወች የስብሰባ ጥሪ አለማድረጉን እናሳዉቃለን።
እንዲሁም በግልም ሆነ በአደረጃጀት ደረጃ ባልተሳተፍንበት በዛሬው ውይይት የሚወሰን ማናቸውም ጉዳይ የአማራ ሕዝባዊ ኃይልን (ፋኖ)- APF የማይመለከት መሆኑን እናሳውቃለን።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!
ጥር 06 ቀን 2014 ዓ.ም
ባሕር ዳር-ኢትዮጵያ