ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) የኮሮና ተህዋሲ እያደረሰ ያለውን ምጣኔ ኃብታዊ ጫና ምክንያት በማድረግ ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች ግማሽ ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የምግብ እህል ለማከፋፈል እየተንቀሳቀሰ ባለበት ወቅት አመራሮቹና አባላቱ ታስረዋል፡፡
–
ፖሊስ አመራሮች ያሰረው “ከላይ በመጣ ትዕዛዝ” መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ እርዳታውንም ተይዟል። የፓርቲውን ፕሬዚደንት እስክንድር ነጋን ጨምሮ ከ15 በላይ አመራሮችና አባላት በአሁኑ ጊዜ በኮልፌ ቀራኒዮ፤ ካራ ቆሬ ፖሊስ ጣቢያ ታስረዋል፡፡
–
የእርዳት እህል ጭነው የነበሩት ሁለት አይሱዙ ተሸከርካሪዎችም ከነጭነታቸው በፖሊስ ተወስደዋል፡፡
–
ጠበቃዎችና ሌሎች አመራሮች ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ፖሊስ ጣቢያው አምርተዋል፡፡
–