በኢትዮጵያ 28 ሚሊየን ሰዎች በኮሮና ሊያዙ ይችላሉ

በኢትዮጵያ 28 ሚሊየን ሰዎች በኮሮና ሊያዙ ይችላሉ – የመንግስት የአደጋ ዝግጁነት ሰነድ

ዋዜማ ራዲዮ– የኮሮና ቫይረስን ስርጭትና ጉዳት ለመገመት በመንግስት በተሰራ የአደጋ ዝግጁነት ቀመር በኢትዮጵያ 28 ሚሊየን ያህል ሰዎች በቫይረሱ ሊያዙ እንደሚችሉ ዋዜማ ያገኘችው ሰነድ ያመለክታል።

የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት በጋራ ባዘጋጁት በዚህ 22 ገፅ ሰነድ በከተሞች አካባቢ ያለው ማህበረሰብ ሙሉ በሙሉ ማለትም 23 ሚሊየን ያህሉ ለወረርሽኙ ተጋላጭ ነው።

50 በመቶ የገጠር ነዋሪ ማለትም 43 ሚሊየን ያህል ህዝብ ለወረርሽኙ የመጋለጥ አደጋ ያንዣበበበት ነው።

ይህ ጥናት የከፋ ሁኔታ ቢከሰት የሚለውን ታሳቢ አድርጎ የተዘጋጀ ሲሆን የተለያይዩ የመከላከያ መንገዶች ተግባራዊ ተደርገውና መንግስት ባለው አቅም ተረባርቦም ቢሆን 28 ሚሊየን የሚጠጋ ሰው በቫይረሱ ሊጠቃ ይችላል። ይህ ጥናት ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ የተጠናቀረ ሲሆን የቀጣዮቹ ሶስት ወራትን የታማሚዎች ቁጥር በየወሩ ከፋፍሎ አስቀምጧል።

የመጀመሪያው ወር

194,104 ስዎች ሊታመሙ ይችላሉ ከነዚህ ውስጥ 9,700 ያህሉ ፅኑ (ICU) ታማሚዎች እንደሚሆኑ መረጃው ያሳያል። 6, 600 የሞት አደጋም ሊያጋጥም ይችላል። ሀገሪቱ ባላት ውሱን የላብራቶር ምርመራ አቅም 1, 242 የሞት አደጋዎችን ብቻ በምርመራ መለየት ሲቻል የቀሩት የሞት አደጋዎች ወደ ምርመራ ሳይደርሱ ምክንያታቸው ኮኖና መሆኑ ሳይረጋገጥ የሚከሰቱ ሊሆኑ ይችላሉ።

በሁለተኛው ወር

211,750 የቫይረሱ ተጠቂዎች እንደሚኖሩ ሲገመት 10,588 ያህሉ በፅኑ (ICU) ታማሚዎች ናቸው። 7,200 የሞት አደጋ ሊያጋጥም ይችላል። 1,355 የሞት አደጋዎች በላብራቶር በተደረገ ምርመራ የተረጋገጠ የኮሮና ቫይረስ ጋር የተያያዘ ሆኖ ይመዘገባል።

በሶስተኛው ወር

232,925 ህሙማን የሚኖሩ ሲሆን 11,646 ያህል ፅኑ (ICU) ታማሚዎች ይኖራሉ። 7, 900 ያህል የሞት አደጋ የሚኖር ሲሆን 1,491 በምርመራ የተረጋገጠ የሞት አደጋ እንደሚያጋጥም የጤና ሚኒስቴርና የኣኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት ትንበያ ይናገራል።

ችግሩን ለመጋፈጥ ዘርፈ ብዙ እርምጃዎች እንደሚይስፈልጉ የተነተነው ሰነዱ ከፖለቲካ አመራር ጀምሮ በክልሎችና በፌደራል መንግስቱ እንዲሁም በተቋማት መካከል ከፍተኛ መናበብ እንደሚያስፈልግ አብራርቷል።

ቀዳሚው እርምጃ በሽታውን መከላከል ላይ ያተኮረ መሆን እንዳለበትና ይህን ተግባራዊ ለማድረግም ሳይንሳዊና ፈጣን እርምጃ የዜጎችን ህይወት እንደሚታደግ ይመክራል።

ከ14 ቢሊየን ብር በላይ የገንዘብ ወጪ ለዚህ የመከላከል ዘመቻ እንደሚያስፈልግም በሰነዱ ተብራርቷል። ትንበያው ይሆናልን ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን በመመልከት ሊከለስ እንደሚችል ሰነዱ ያሳስባል።አንዳንድ ሙያዊ መስፈርቶችንም እንዳልተገበረ ጥናቱ አምኗል። የሰነዱን ጨመቅ ከታች ይመልከቱ [ዋዜማ ራዲዮ]

…………………………………………………

Health Ministry projections seen by POLITICO outline a worst-case scenario for Ethiopia predicting that 28 million people are at risk of contracting the virus. Health officials are now working on the assumption that in a worst-case scenario Ethiopia could already be an incubator for a “super-spreading event” and that the health system will be “overwhelmed in a few weeks.” A shortage of medical oxygen supplies is one major concern.

Abiy has told world leaders and senior politicians in a flurry of recent phone calls of the risk African countries face from civil unrest should a disruption to supply chains lead to food shortages, said a senior EU diplomat. “Abiy and Macron are on the same page,” said a senior EU diplomat briefed on the call between the two leaders. Abiy’s office did not reply to several requests for comment.

But Mamo Mihretu, a senior adviser to the prime minister, said the global consensus around an aid package to Africa was growing fast.

https://www.politico.com/news/2020/04/01/g-20-prepares-coronavirus-rescue-package-for-africa-160867