Blog Archives

የድንበር ጉዳዮች ትኩረት ይሻሉ (ተፈሪ መኮንን )

ባለፈው ሣምንት በሰሜን ምዕራብ እና በደቡብ ኢትዮጵያ በሚገኙ ሁለት የጠረፍ ከተሞች በተለያዩ መነሾዎች የተከሰቱት ጠንከር ያሉ ግጭቶች በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት ማስከተላቸው ሰምተናል፡፡ እነዚህ ግጭቶች የተከሰቱት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተዘጋጀው የጠረፍ ከተሞችን ችግሮች የመዳሰስ እና የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን የመቀመር ዓላማ ይዞ የተካሄደው አውደ ጥናት በተጠናቀቀ ማግስት ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ሞያሌ፣ ቋራ እና መተማን ከመሳሰሰሉ የጠረፍ ከተሞች የመጡ ሰዎች ተሳታፊዎች በዚሁ ጉባዔው ተሳታፊ እንደነበሩ እና ከአዲስ አበባ ወደ መጡበት በመመለስ ሳይ ሳሉ ነበር ግጭቶቹ ተከሰቱት — የመተማው ግጭት ሰኔ 27 2010 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሞያሌው ደግሞ በማግስቱ ሰኔ 28 2010 ዓ.ም፡፡ በቋራ እና መተማ አካባቢ የተከሰተው ግጭት በመከላከያ ኃይል ጣልቃ ገብነት ቢቆምም፣ ግጭቱን ለዘለቄታው ለመፍታት እንዲያስችል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ለሱዳን ፕሬዚዳንት ኦማር ሐሰን አል በሽር የላኩትን መልዕክት መላካቸው ታውቋል፡፡ ከቋራ እና መተማው ግጭት አንድ ቀን ቀደም ብሎ ውጥረት ተለይቷት በማታውቀው የኢትዮጵያ ሞያሌ ከተማ የተከሰተው ጎሣን መሠረት ያደረገ ግጭት መሆኑን እና የመተማው ደግሞ ከእርሻ መሬት ጋር የተያያዘ እንደሆነ የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የጠቀሱ ሲሆን፤ ከሁለቱ ከተሞች የመጡት የጉባዔው ተሳታፊዎች በስብሰባው ላይ ከሰጡት አስተያየት መረዳት እንደሚቻለው ግጭቶች በተደጋጋሚ ይከሰታሉ፡፡ የድንበር ነገር ከህገ ወጥ ንግድ፣ ከህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ ከጸጥታ ወዘተ ጋር የሚያያዝ ብቻ ሳይሆን፤ ሥር የሰደደ ከታሪክ ጋር የተያያዘ ችግር የሚታይበት ነው፡፡ በዚህ የተነሳ በወዲያኛው ሣምንት መጨረሻ
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ቦረና ውስጥ በአሰቃቂ ሁኔታ የሰው ሕይወት እየተቀጠፈ ነው ፤ የመከላከያ ሰራዊት ዳር ቆሞ እየተመለከተ ነው።

ቦረና ውስጥ የሰው ሕይወት እየተቀጠፈ ነው። የትኛውም ሚዲያ ሆነ የመንግስት ባለስልጣን ስለ ጉዳዩ ሲናገርና መፍትሄ ለመስጠት ሲንቀሳቀስ አላየሁም። በተለይ ላለፉት ሦስት ቀናት ከአከባቢው በደረሰኝ መረጃ በሞያሌ ከተማና አከባቢው እየሆነ ያለው ነገር በጣም አሰቃቂ ነው። በአከባቢው የሚኖሩ ሰዎች በስልክና በፌስቡክ “ኧረ ስዩም ስለ ቦረና ምነው ዝም አልክ?” እያሉ ይጠይቁኛል። ከእነዚህ ውስጥ ለብዙ አመት የማውቀውን ወዳጄን “እስኪ በአከባቢው ስለ ተከሰተው ግጭት የሚያሳይ ፎቶ ወይም ቪዲዮ ላክልኝ?” ብዬ ጠየቅኩት። ይህ ወዳጄ በአንድ ግዜ ከአስር የሚበልጡ የፎቶ ምስሎች ላከልኝ። በሞያሌ አከባቢ በተከሰተው ግጭት ምክንያት የተገደሉና የቆሰሉ ሰዎችን ምስል ከአንድ ደቂቃ በላይ መመልከት አልቻልኩም። እኔ ለመመልከት የከበደኝ ነገር የአከባቢው ነዋሪዎች በእውን እየሆኑት ነው። በዚህ መልኩ በጥይት እየተገደለ ላለ ሕዝብ ስለ ፍቅርና ይቅርታ መናገር በሰው ሕይወት እንደ መቀለድ ነው። የቦረና አከባቢ ነዋሪዎች በየቀኑ በጥይት እየተገደሉ ነው። ነዋሪዎቹ በጥይት ሲገደሉ የመከላከያ ሰራዊት ዳር ቆሞ እየተመለከተ ነው። ይሄ ነገር መቆም አለበት! ጠ/ሚ አብይ ሆነ ኦቦ ለማ መገርሳ በቦረና እየደረሰ ያለውን ግድያ ማስቆም አለባቸው። ግድያውን ሳያስቆሙና ገዳዮችን ለፍርድ ሳያቀርቡ ለቦረና ሕዝብ ስለ ይቅርታና ፍቅር፣ ስለ ሰላምና ዴሞክራሲ መናገር አይችሉም። ማንም ሆነ ምንም ነገር ከሕይወት አይበልጥም። የሰው ልጅ ሕይወት ምርጫና አማራጭ የለውም። ሕይወት በፍቅርና ይቅርታ የሚገኝ ነገር አይደለም። ፅሁፍ ስዩም ተሾመ  …. ምስል ከሀምዛ ቦረና
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ኮማንድ ፖስቱ በሞያሌ ከተማ ትጥቅ እያስፈታ መሆኑ ታወቀ

ራሱን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መመሪያ አስፈጻሚ እያለ የሚጠራው ኮማንድ ፖስት ትጥቅ እያስፈታ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡ እንደ ግብረ ኃይሉ ገለጻ ትጥቅ የማስፈታት እንቅስቃሴ እየተደረገ ያለው በዋነኝነት በሞያሌ ከተማ ሲሆን፤ በተጨማሪም በሌሎች አካባቢዎችም ትጥቅ የማስፈታት እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል፡፡ እሁድ ሚያዝያ 28 ቀን 2010 ኢትዮጵያ እና ኬንያ በሚዋሰኑበት ሞያሌ ድንበር አካባቢ፣ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል እና በኦሮሚያ ፖሊስ አባላት መካከል ረዥም ሰዓት የወሰደ የተኩስ ልውውጥ መደረጉን መዘገባችን ይታወቃል፡፡ በዕለቱ ከረፋዱ አምስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ አንድ ሰዓት ድረስ በተደረገው በዚሁ የተኩስ ልውውጥ፣ ከሁለቱም ወገኖች የሞት እና የመቁሰል ጉዳት ደርሷል፡፡ ይህን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት መግለጫ ያወጣው ኮማንድ ፖስት፤ የተካሄደውን የተኩስ ልውውጥ፡- “በሁለት ጎራዎች የታጠቁ ኃይሎች መካከል ማኅበረሰቡን ዒላማ ያደረገ በመጠኑም ሰፋ ያለ ግጭት ተከስቶ በሰው ህይወት ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡” ሲል ገልጾታል፡፡ በተከሰተው ግጭትም “የሰው ህይወት ጠፍቷል፤ የመቁሰል አደጋም ደርሷል፡፡” ሲል አክሏል፡፡ የተኩስ ልውውጡ የተካሄደው በሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል እና በኦሮሚያ ፖሊስ አባላት መካከል መሆኑ ቢታወቅም፤ ኮማንድ ፖስቱ ግጭቱን ‹‹በሁለት ጎራዎች የታጠቁ ኃይሎች መካከል የተካሄደ›› ሲል መግለጹ ግራ አጋቢ እንደሆነ ተነግሯል፡፡ እሁድ ዕለት በሁለቱ ክልሎች የፖሊስ አባላት መካከል የተካሄደውን የተኩስ ልውውጥ ተከትሎ በዛሬው መግለጫው፣ ትጥቅ የማስፈታት እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቀው ኮማንድ ፖስቱ፤ እስካሁን ድረስም የተለያዩ የመሳሪያ ዓይነቶችን መንጠቁን ተናግሯል፡፡ ግብረ ኃይሉ ከፖሊስ አባላት እጅ መሳሪያ እየነጠቀ መሆኑን በይፋ ባይገልጽም፤ መረጃዎች ግን በሞያሌ የሚገኙ ለጊዜው ቁጥራቸው
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አፈፃፀም የሚከታተለው መርማሪ ቦርድ የሞያሌውን ግድያ ማጣራቱን እንዲያቆም ታዘዘ

ዋዜማ ራዲዮ- በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ሞያሌ ከተማ በመከላከያ ሰራዊት አባላት ስለተገደሉት ዜጎች ጉዳይ እንዲያጣራ የተሰየመውና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አፈፃፀም የሚከታተለው መርማሪ ቦርድ የማጣራት ተልዕኮውን እንዲያቋርጥ መታዘዙን የዋዜማ ምንጮች አመለከቱ። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተቋቋመው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርዱ ስብሳቢ በአቶ ታደሰ ወርዶፋ የሚመራውና አስራ ሁለት አባላትን ያካተተው መርማሪ ቡድን ከመጋቢት 16 እስከ መጋቢት 24 ድረስ ወደ ሞያሌ ተጉዞ ምርመራ የማካሄድ እቅድ ነበረው። ይሁንና መጋቢት 16 የመርማሪ ቡድኑ አባላት ወደ ሞያሌ ለመጓዝ በተሰባሰቡበት ወቅት “ከበላይ የመጣ ትዕዛዝ”  ነው በሚል ከጉዟቸው እንዲመለሱ መደረጋቸውን የቡድኑ አንድ አባል ይናገራሉ። “የተወሰነው ጉዞውን መቀጠል አለብን አንመለስም ስንል ሌሎች ደግሞ መመለስ አለብን ስላሉ ጉዞው ሳይካሄድ ቀርቷል” ይላሉ ለዋዜማ ጉዳዩን ያሰረዱት አባል። የመርማሪ ቡድኑ እንዲመለስ የትኛው ባለስልጣን ትዕዛዝ እንደሰጠ እንደማያውቁም ይናገራሉ። ቡድኑ ወደ ሞያሌ ተጉዞ ከሟች ቤተሰብ፣ ከቁስለኞች እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመነጋገርና መረጃ በማሰባሰብ በመከላከያ ሰራዊቱ ስለተገደሉት ዜጎች አጣርቶ ለመምጣት ተልዕኮ ነበረው። ከዚህ በኋላ መርማሪ ቡድኑ ስራውን ይቀጥል እንደሆነ አባላቱ ብዙም ተስፋ አያደርጉም። የመከላከያ ሰራዊቱ አባላት በመረጃ ስህተት ነው በሚል ቢያንስ ዘጠኝ ሰዎች ገድለው አስራ ሶስት ያቆሰሉ ሲሆን ስምንት ሺ ያህል ወገኖች ደግሞ ወደ ኬንያ ተሰደዋል። ድርጊቱ በርካቶችን ያስቆጣ ሲሆን መንግስት ድርጊቱን የፈፀሙትን የሰራዊቱ አባላት ትጥቅ አስፈትቶ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ተናግሯል። የሰራዊቱ አባላይ የኦነግ ታጣቂዎች በድንበር በኩል ጥሰው ገብተዋል የሚል መረጃ ደርሶት ለወታደራዊ ግዳጅ
Tagged with: ,
Posted in Ethiopian News