Blog Archives

ዶክተር አብይ አሕመድ ግጭት ወደባሰበት ደቡብ ክልል ሕዝቡን ለማነጋገር ሊያቀኑ ነው ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከህብረተሰቡ ጋር ለመወያየት ቀጣይ ሳምንት ወደ ደቡብ ክልል ያቀናሉ በአገሪቱ አንዳንድ አከባቢዎች በተለይም ደግሞ በሀዋሳና ወላይታ ሶዶ የተነሱትን ግጭቶች ከህብረተሰቡ ጋር በመወያየት ለመፍታት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በቀጣዩ ሳምንት ወደ ስፍራው እንደሚያቀኑ ገለጹ፡፡ እስከዚያ ድረስ ግን በሰላምና ፍቅር የምትታወቀው የትንሿ ኢትዮጵያ የደቡብ ክልል ነዋሪዎች፣ የአከባቢው ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች፣ ለአካባቢያቸው ሰላም በጋራ እንዲሰሩ ጠይቀዋል፡፡ የጸጥታ አካላትም ህብረተሰቡን ባሳተፈና እና ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ የየአካባቢውን ሰላም ለማስጠበቅ እንዲሰሩ ጠይቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ክልል እንሁን በሚል ለሚነሱ ጥያቄዎች ሕገ መንግስቱ ስርዓት ያስቀመጠ በመሆኑ ሁሉንም ነገር በሰላም መጠየቅና ማስተናገድ እንደሚቻልም ገልጸዋል፡፡ ከወሰን ጋር በተያያዘ በተለያዩ አከባቢዎች የሚነሱ ጥያቄዎችን በጥናት መመለስ ይቻል ዘንድ ይህንን የሚከታተል ኮሚሽን ለማቋቋም መንግስት እያሰበ መሆኑንም ዶ/ር አብይ ገልጸዋል፡፡ ይህ ኮሚሽን ከየአከባቢው የሚነሱ ጥያቄዎችን በመቀበል ስር ነቀል መፍትሔ እንደሚሰጥም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ ምንጭ Ebc
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ሲዳማ እና ወላይታ ምን ነካቸው? (አቤ ቶክቻው) 

ሲዳማ እና ወላይታ ምን ነካቸው? (አቤ ቶክቻው) ከፊቼ ጫምባላላ ክብረ በዓል ጀምሮ በሃዋሳ የሚሰማው ወሬ ደስ አይልም፤ ሲዳማ እና ወላይታ አንተ አንተ እየተባባሉ እየተጣሉ ከጸብም አልፎ ደም መፋሰስ ደረጃም እንደደረሱ እየተሰማ ነው! ያሳዝናል! ጫምባላላ የሚከበረው ለእርቅ እና ለሰላም ነው! የፍቼ ጫምባላላ ዕለት የተጣላ ይታረቃል አዲሱ አመት የፍቅር እንዲሆን ሽማግሌዎች ይመርቃሉ ወጣቶች ያዜማሉ ነበር… የተነገረን… ነገር ግን እየተሰማ ያለው በተቃራኒው ሆኗል። ከ እለተ ፍቼ ጫምባላላ አንስቶ ዛሬም በሃዋሳ አየሩ ደስ የማይል እንደሆነ ወዳጆች እየነገሩን ነው! የክልሉ መንግስት የፍቅር ከተማይቱ ሃዋሳ ወደ ግርግር መዲናነት እንዳትለወጥ አፋጣኝ ምላሽ መስጠት አለበት። የፌደራል መንግስቱም ቢሆን እንዲህ አይነት ነገሮችን በቶሎ ለማስቆም ካልተጋ ይሄ የዘረኝነት እና ጎሰኝነት በሽታ ከአተት የበለጠ ተዛማች ነው እና ብዙ ጥፋት ሊያጠፋ ይችላል! ትላንት ከወደ ወልቅጤ ስንሰማው የነበረውም ነገር ተመሳሳይ ነው… በስራ ወዳድነት እና በሰላማቸው የሚታወቁት የደቡብ ሰዎች በየዘራቸው እንጋጭ ካሉ ማቆሚያው ከባድ ነው! ትንሿ ኢትዮጵያ ደቡብ የምናውቅሽ በፍቅር ከተማነት ነው… እግዜር ሰላምሽን ይመልሰው!
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በአዋሳ የብሔር ግጭት ተባብሶ ቀጥሏል ።

አሳዛኝ ዜና በወላይታ የህዝብ አመፅ ተቀስቅሷል ። ውጥረቱ ቀጥሏል። በየሀገሪቱ ክፍል መሞታችን ይብቃ !!! ለአንድነት ብለን ዝም ባልን ስቃያችን በዛ ከዚህ በኋላ የመጣውን ሁሉ ለመቀበል ዝግጁ ነን። በማለት ተቃውሞ እያሰሙ ይገኛሉ ። አዋሣ ከትላንት ጀምሮ ኔትወርክ መብራት ውሀ የለም በከተማው ውሥጥ ግልፅ ዝርፊያና ግድያ ተንሠራፍቷል። የሲዳማ ወጣቶች ወላይታዎችን እያሣደዱ በአሠቃቂ ሁኔታ እየገደሉ ነው፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን የክልሉ ፖሊሶች በዝምታ እያለፉ ነው፡፡ አንድ የፌስቡክ አክቲቪስት የሚከተለውን ፅፏል ። በሃዋሳ ዛሬም ዉጥረቱ እንቀጠለና ተኩስ እንደሚሰማ ጠዋት አንድ ሰዕት (በኢትዮጵያ) አከባቢ ያነጋገርኩት የቀድሞ የስራ ባልደረባዬ የሆነ የሃዋሳ መምህራን ኮሌጅ መምህር አሳዉቆኛል። በትላንት ዕለትም የአንድ የኮሌጁ ተማሪ አስክሬን እንዳየና በርካታ የቆሰሉ ደግሞ ወደ ሃዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል መጫናቸዉን አረጋግጦልኛል። የሞቱት ተማሪዎች ሶስት መሆናቸዉን የሚናገሩም አሉ። አንዱ ሟች ተማሪ የሲዳማ ዞን በንሳ አከባቢ ተወላጅ መሆኑን ጨምሮ ገልፆልኛል። ከዚያ የጠዋት ስልክ በኻላ በርካታ የመንግስት ባለስልጣናትና የሆስፒታል ምንጮች ጋር ብደዉልም ስልክ ሊሰራልኝ አልቻለም። በአሁኑ ሰዕት በሃዋሳ የስልክ አገልግሎት ተቋርጧል የሚል ግምት አለኝ። ትላንትና ማምሻዉን በሃዋሳ ዩንቨርስቲ ዉጥረት እንደነበር ሰምቻለዉ። የዉጥረቱ መንስኤም ከወላይታ ሶዶ ዩንቨርስቲ የሲዳማ ልጆች ተባረዋል ወይም ፈርተው ወተዋል የሚል ዜና ከተሰማ በሃላ መሆኑን ምንጮቼ ነግረዉኛል። እንደሚታወቀዉ ሃዋሳ ከ ማክሰኞ ጀምሮ በ ግጭት ዉስጥ ስትሆን የሰዉ ነብስና ከፍተኛ ንብረት ጠፍቷል። ግጭቱን የከፋ የሚያደርገዉ የብሄር ግጭት መልክ እንዲይዘ የሚሰሩ ወገኖች ከጀርባ መኖራቸዉ ነዉ። እኝህ ወገኖች በሃገር ደረጃ ለተያዘዉ
Tagged with:
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በሀዋሳ ውጥረቱ ቀጥሏል – ጸጥታ አስከባሪዎች ዝም እንዲሉ ተደርጓል።

በሀዋሳ ውጥረቱ ቀጥሏል። ጨንበላላን ለማክበር በወታው ሕዝብ ላይ ሕወሓት ቅጥረኞቹን ሽፈራው ሽጉጤንና አሽከሮቹን አሰማርቶ በፈጠረው አምባጓሮ በርካታ ዜጎች ተጎድተዋል። በሲዳማና በወላይታ መካከል ግጭት እንዲከሰት በሕወሃት ትእዛዝ የታጠቁ ሽፈራው ሽጉጤ ያሰማራቸው ካድሬዎች በፈጠሩት ችግር ምክንያት ግጭቱ ቀጥሎ ሰላማዊዋ ሀዋሳ በጥይት ስትናጥ ውላለች። ጸጥታ አስከባሪዎች ዝም እንዲሉ ተደርጓል። ጸጥታ አስከባሪዎች የተሰማሩት ግጭቱ ካለበት ቦታ ይልቅ ባሌለበት ቦታ መሆኑን ታዛቢዎች ይናገራሉ። እነ ሽፈራው ሽጉጤ የህወሃት የእንጀራ ልጆች የዘሩት የዘረኝነት ውጤት ነው።በተለይም በወላይታውና ሲዳማው መካከል ግጭቱ ቀጥሏል። በጉራጌ ክልልም ወልቂጤ ላይ በቀቤናና በጉራጌ መካከል ግጭት እንዲነሳ እሳቱን የለኮሱት ሽፈራው ሽጉጤ የላካቸው የታጠቁ ሐይሎች መሆናቸው ተረጋግጧል።
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News