Blog Archives

ወንጀልን ለማቆንጀት፣ ሰበብና ማመካኛ መደርደር ይብቃ! ( ዮሃንስ ሰ )

• አለዚያ፣ ህግና ስርዓት፣ ለጉልበት ወይ ለትርምስ ተሸንፎ ማጣፊያው ያጥረናል። • “የሕዝቡ ጥያቄ ስላልተደመጠ ነው” ብሎ ያሳብባል አንዱ ምሁር። (ጥፋትና ጭካኔን የሚያስውብተዓምረኛ እውቀት የያዘይመስል።) • “መንግስት ፈጣን ምላሽ ስላልሰጠ ነው” ይላል አንደኛው ፀሐፊ ። (ክፋትንና ምቀኝነትን የሚያቆነጅ ልዩ አስማት ያገኘ ይመስል።) • “የመወያየትና የመነጋገር እድል ስለሌለ ነው” ይላል አንደኛው ፖለቲከኛ (በዚህች ንግግሩ፣ ወንጀልን እንደፍትህ የሚቆጠርለት ይመስል።) በአሉባልታ ጭፍን ጥላቻንና ዛቻን የሚዘሩ፣… የሰውን ንብረት የሚዘርፉና የሚያቃጥሉ፣… ሰውን ከመኖሪያው የሚያሳድዱና የሚገድሉ ወንጀለኞችን ለማቆንጀት፣ እንደበቀቀን ነጋ ጠባ፣ ማሳበቢያ ቃላትን ማነብነብ፣ ማመካኛ አባባሎችን ሌት ተቀን መደጋገም ይብቃ! የስንቱ ሕይወት ጠፋ? የስንቱ አካል ጎደለ? ሚሊዮኖች ተፈናቅለው፣ ንብረታቸው ተዘርፎና ወድሞ፣ ኑሯቸው ሲናጋ፣ እለት በእለት እያየንም እንኳ፣ ትንሽ ሰከን ብለን ማሰብ አንጀምርም? አሁንም ሰበብ አስባብ መደርደር? መነሻው፣ ምንም ይሁን ምን፣ ጭፍን እምነትም ይሁን ሌጣ አላዋቂነት፣… ፖለቲካን እንደቁማር ጨዋታ የማየት ሞኝነትም ይሁን የአእምሮ ድንዛዜ፣ የዘረኝነት በሽታም ይሁን አልያም ሌላ መነሻም ይኑረው፣… የወንጀል ድርጊትንና ጥፋትን ለማቆንጀት፣ እንደ ልማዳዊ የእለት ስራ፣ ልማዳዊ ሰበቦችና ማመካኛዎች፣ በበቀቀን ደመነፍስ እየተነበነቡ፣ በሰላም መቀጠል አይቻልም – ወደባሰ ጥፋት ነው የሚያወርዱን። “ይሄኛው ጥያቄ ተገቢ ነው። ያኛው አቤቱታ ትክክለኛ ነው። ተሰሚነት ማግኘት አለባቸው። መንግስት ተገቢ ጥያቄዎችን ካላደመጠ፣ ባለስልጣን ትክክለኛ አቤቱታዎችን ካልሰማ፣ ትልቅ ጥፋት ነው። በዚያ ላይ፣ ለአጥፊ ወንጀለኞች መንገድ ይከፍታል” ብሎ ማብራራት አንድ ጉዳይ ነው። እንዲሁ የምበደፈናው፣ “የህዝብ ጥያቄ” እያሉ ማነብነብ ግን፣ ጤናማ አስተሳሰብ አይደለም። በዚያ ላይ፣
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ዐቃቤ ሕግ በዐቃቤ ሕግ ላይ ያቀረበው የ”ሀሰት ክስ” መነጋገሪያ ሆነ ።

ዐቃቤ ሕግ በዐቃቤ ሕግ ላይ ያቀረበው የ”ሀሰት ክስ” ይህ ማመልከቻ ረዥም ነው። ታግሳችሁ እንድታነቡት ጋብዣችኋለሁ! የቂሊንጦ እስረኞች ዘንድ መነጋገሪያ የሆነ ክስ ነው! ዐቃቤ ሕግ በዐቃቤ ሕግ ላይ ያቀረበው የ”ሀሰት” ክስ ነው (ጌታቸው ሽፈራው) ቀን 11/11/2010 ዓ.ም የወ/መ/ቁ. 203074 የማ/መ/ቁ. 05968109 በኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ለክቡር ዋና ዐቃቤ ህግ አዲስ አበባ አመልካቾች፡- 1ኛ. አቶ አበበ ብርሃን የወ/አይነት ሙስና 2ኛ. አቶ በላይነህ ፈንታ የፍ/ዐክ ቀጠሮ 3ኛ. አቶ አብዮት ተስፋየ ጉዳዩ፡- ክስ እንዲቆረጥልኝ አቤቱታ ማቅረብን ይመለከታል እኛ አቤቱታ አቅራቢዎች በወ/መ/ቁ 203074 የሙስና ወንጀል ፈጽማችኋል በሚል የሀሰት ክስ ቀርቦብን በአዲስ አበባ የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የምንገኝ ሲሆን የተፈጸመብንን በደል በመዘርዘር ፍትህ ይሰጠን ዘንድ አቤቱታችንን እንደሚከተለው እናቀርባለን፡፡ 1ኛ አመልካች በፌዴራል ጠቅላይ ዐ/ህግ የኢኮኖሚ ጉዳዩች ዐ/ህግ ሆኜ ሳገለግል የነበረሁ፤ 2ኛ አመልካች በግል ሥራ (በኢንቨስትመንት ማማከርና ንግድ) ላይ የተሰማራሁና ለባለፉት አራት (4) ዓመታት በውጭ ሀገር ቆይቼ ወደ ሀገሬ በተመለስኩ 2 ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የተከሰስሁ፤ 3ኛ አመልካች ደግሞ በጥብቅና ስራ ላይ የተሰማራሁ ግለሰብ ነኝ፡፡ ተከሳሾች 1ኛ አመልካች ሃምሌ 11/2009 ዓ.ም ከስራ ገበታዬ (በልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ከሚገኘው ቢሮዬ) ከቅርብ የሥራ ሃላፊዬ እና የሥራ ባልደረቦቼ ነጥለው ለሥራ እንፈልግሃለን በሚል ከሥራ ገበታየ ከወሰዱኝ በኋላ ከ1 ቀን በፊት ሃምሌ 10/2009 ዓ.ም ጉቦ ስቀበል እጅ ከፍንጅ እንደተያዝኩ በማስመሰል የሀሰት ዜና በኢቲቪ፣ በሬዲዮ ፋናና በሪፖርተር ጋዜጣ በማሰራት የሀሰት ክስ መስርተውብኛል፡፡ 2ኛ
Tagged with:
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ተድበስብሶ የቀረው የቂሊንጦ ቃጠሎ ጉዳይ (ማሕሌት ፋንታሁን)

ተድበስብሶ የቀረው የቂሊንጦ ቃጠሎ ጉዳይ የአግ7፣ ኦነግ እና አልሻባብ አባል በመሆን እና ተልእኮ በመቀበል ለቂሊንጦ ማረሚያቤት ቃጠሎ፣ ለሰው እና ንብረት መጥፋት ተጠያቂ ናችሁ ተብለው በሽብር ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ 38 እስረኞች እንደነበሩ የሚታወስ ነው። ሚያዚያ 30/2010 በተሰጠው ብይንም 8 ተከሳሾች በነፃ ተሰናብተዋል። 26ት ተከሳሾች ደግሞ አንቀፅ ተቀይሮ በወንጀል ህጉ አንቀፅ 464 (2)ሀ [1ኛ፣ 4ኛ፣ እና 15ኛ ተከሳሾች] ፣ አንቀፅ 464(1)ሐ [14ኛ፣ 16ኛ፣ 19ኛ ፣ 20ኛ፣ 22ኛ እና 23ኛ ተከሳሾች] ፣ አንቀፅ 464(2) ለ [2ኛ፣ 3ኛ፣ 5ኛ፣ 8ኛ፣ 10ኛ፣ 12ኛ፣ 13ኛ፣ 17ኛ፣ 24ኛ፣ 26ኛ፣ 37ኛ እና 38ኛ ተከሳሾች] እንዲሁም አንቀፅ 464 (2) ለ እና 494 (2) [9ኛ፣ 25ኛ፣ 30ኛ፣ 35ኛ እና 36ኛ ተከሳሾች] እንዲከላከሉ ብይን ተሰጥቷል። ብይኑ ከተሰጠ በኋላ 26ቱ ተከሳሾች ክሳቸው የተቋረጠ ሲሆን የተቀሩት 4ት ተከሳሾች (31ኛ፣ 32ኛ፣ 33ኛ እና 34ኛ ተከሳሾች) ደግሞ የወንጀል ህጉን 464(2)ለ ን [የእስረኞች አመፅ መምራት እና የማደራጀት ወንጀል] እና 540 ን [የሰው መግደል ወንጀል] እንዲከላከሉ ተወስኗል። የቂሊንጦ ቃጠሎ፣ የጠፋው የሰው ህይወት እና የንብረት ውድመት አራቱ ተከሳሾች ላይ ብቻ ተደፍድፏል። 31ኛ ተከሳሽ ጌታቸር እሸቴ፣ 32ኛ ተከሳሽ ቶፊቅ ሽኩር ፣ 33ኛ ተከሳሽ ሸምሱ ሰኢድ እና 34ኛ ተከሳሽ ፍፁም ጌታቸው ላይ። እነዚህ አራት ተከሳሾች ተከላከሉ ያስባላቸው እና የተጠቀሰባቸው የምስክሮች ቃል ላይ በተከሳሾቹ ተገለዋል ተብለው በስም የተጠቀሱት አራት እስረኞች ብቻ ናቸው። ማረሚያ ቤቱ ባመነው እንኳን 23 እስረኞች ሞተዋል። ትክክለኛው የሟቾች
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ለዓመታት በርካቶችን ባልተጨበጠ የሽብር ወንጀል ሲከስ የኖረው የኢሕአዴግ አቃቢ ሕግ ከስልጣን ተባረረ።

ዋዜማ ራዲዮ- የፌደራሉ ዋና ዓቃቤ ህግ ጽህፈት ቤት ለዓመታት በርካቶችን ባልተጨበጠ የሽብር ወንጀልና ተያያዥ ከፍተኛ ወንጀሎችን በመክሰስና በማሰፈረድ የሚታወቁትን ዓቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ ወንድማገኝን ከኃላፊነት በማሰናበት በቦታቸው አቶ ፍቃዱ ፀጋን መሾሙን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ዋና ዓቃቤ ህጉ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ አቶ ብርሃኑ ሐምሌ 12፣ 2010 ዓ.ም የመስሪያ ቤታቸውን የለውጥ ሂደት (ሪፎርም) በተመለከተ የተለያዩ ርምጃዎችን ለስራተኞቹ ያስተዋወቁ ሲሆን በአቶ ብርሃኑ ወንድማገኝ ሲመራ የነበረውን ጭምሮ የበርካታ ዳይሬከቶሬት ኃላፊዎችን በማንሳት በአዲስ እንደተኩ የውስጥ ምንጮች ለዋዜማ አረጋግጠዋል፡፡ አቶ ብርሃኑ ወንድማገኝ ለዓመታት የሽብርና የተደራጁ ድንበር ተሸጋሪ ወንጀሎች ዳይሬክተር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን የዚሁ የፌደራሉ መንግሰት ዋና ዐቃቤ ህግ ጽህፈት ቤት ቁልፍ ሰዎች አንዱ እነደነበሩ ይነገርላቸዋል፡፡ በርካታ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችንና አባላቶቻቸውን እንዲሁም የመብት አቀንቃኞችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ጦማሪዎችንና የተለያዩ ግለሰቦችን የመንግሰት አቃቤ በመሆን በተለያየ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች በሽብርና በሌሎች ከባድ ወንጀሎች ክስ በመመስረትና በማሰፈረድ ይታወቃሉ፡፡ እንዲሁም በሰብዓዊ መብት ጉዳይ በበጎ የማይንሳው አቶ ብርሃኑ ወንድምአገኝ በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በእስር የሚገኙ ተከሳሾችን የፍርድ ሁደት በማጓተትና በእስር የሚገኙ ታራሚዎች የመብት ጥሰት እዲፈጸምባቸው ተደጋጋሚ ምክንያት ይሆኑ እንደነበርም ወቀሳ ሲሰማባቸው ይሰማል፡፡ ዋና ዓቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ ጸጋዬ በጻፉት የሹመት ደብዳቤ አቶ ፍቃዱ ጸጋ የተባሉ ነባር የህግ ባለሙያ አቶ ብርሃኑ ወንድምአገኝን እንዲተኩ ማድረጋቸውንና አቶ ተመስገን ላጲሶን በምክትል ዳይሬከተር መሾማቸውን የዋዜማ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ሌሎች በርካታ ሀላፊዎችም በአዳዲስ የተተኩ ሲሆን ለሹም ሽር ምክንያት የሆነው የቀደሙት ሀላፊዎች
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በአርበኞች ግንቦት ሰባት ተከሰው እስካሁን እስር ቤት የሚገኙት ተከሳሾች ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቀረቡ።

በአርበኞች ግንቦት ሰባት ተከሰው እስካሁን እስር ቤት የሚገኙት ተከሳሾች ለፍርድ ቤት ያቀረቡት አቤቱታ የመዝገብ ቁጥር 192368 ሐምሌ 10 ቀን 2010 ዓ/ም ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት አዲስ አበባ ከሣሽ የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ 2ኛ ተከሣሽ አቶ ግርማ ፍቃዱ ሞላ 33ኛ ተከሣሽ አቶ ሀብቶም ማማይ 3ኛ ተከሣሽ አቶ እሸቴ ዘለቀ መኮነን 38ኛ ተከሣሽ አቶ ገብረኪዳን መልካሙ አያሌው 4ኛ ተከሣሽ አቶ ለማ እሸቱ ዘገደ 42ኛ ተከሣሽ አቶ ሲሣይ መኮንን በቀለ 5ኛ ተከሣሽ አቶ አብርሃም ደርበው 43ኛ ተከሣሽ አቶ ወንድይፍራው አደራጀው ካሣይ 6ኛ ተከሣሽ አቶ መስፍን ሁሬሣ ተክሌ 49ኛ ተከሣሽ አቶ ላመነው ማሞ አለፈ 8ኛ ተከሣሽ አቶ ፀጋየ እሸቴ መኩሪያ 53ኛ ተከሣሽ አቶ ፍሬው ሞኝነት ካሣ 13ኛ ተከሣሽ አቶ ደሣለኝ ንጉሤ ሙላቱ 56ኛ ተከሣሽ አቶ ሰሎሞን አያሌው ዘነበ 14ኛ ተከሣሽ አቶ ሀብሉ አንገሶ ውንዴሣ 64ኛ ተከሣሽ አቶ እልፈቱ ፋሲካው ውብነህ 15ኛ ተከሣሽ አቶ በዛ ሙላው ውብነህ 68ኛ ተከሣሽ አቶ ሀብታሙ መለሰ ይርና 16ኛ ተከሣሽ ቴወድሮስ ይግዛው አራጌ 69ኛ ተከሣሽ አቶ ዓለሙ አለልኝ ብርሃኑ 18ኛ ተከሣሽ አቶ ገነቴ ተረፈ ዓለሜ 71ኛ ተከሣሽ አቶ ወርቁ ሞገስ ድረስ 20ኛ ተከሣሽ አቶ ደሴ ኃይሌ ጣሰው 73ኛ ተከሣሽ አቶ ነጋሽ መሐመድ ሀቢብ 25ኛ ተከሣሽ አቶ ግደይ ፀሐየ ይግዛው 75ኛ ተከሣሽ አቶ አሸናፊ አብርሃ ይርጋ 26ኛ ተከሣሽ አቶ ሰሎሞን እሸቴ ጌታሁን 76ኛ ተከሣሽ ረ/ሣ መኳንንት ዓለሙ መለሰ
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በውጭ ጉዳይ ቀላቀባይ አቶ መለሰ አለም ተደበደብኩ ያለው ተከሳሽ በድብቅ ተፈርዶበታል

በውጭ ጉዳይ ቀላቀባይ አቶ መለሰ አለም ተደበደብኩ ያለው ተከሳሽ በድብቅ ተፈርዶበታል (ፍሬው ተክሌ) የተከሰሰበት ጉዳይ በልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት 19ኛ ወ/ችሎት ሲከታተል የነበረው ሶሬሳ ሰይፉ አለሙ ዛሬ ግንቦት 22/2010 ዓም በድብቅ 16 አመት ተፈርዶበታል። ዳኞች የተሟሉ ቢሆንም “የአንተን ጉዳይ በቢሮ በኩል ነው የምናየው” ብለው በችሎት ተላላኪ በኩል ጥሪ ቢያቀርብለትም “የኔ ጉዳይ በታዛቢ በኩል ነው መታየት ያለበት እንጂ በድብቅ አይደለም። በቢሮ በኩል አልቀርብም በማለት መልስ ሰጥቷል” ዳኞቹም ተከሳሹ ባልቀረበበት የ16 አመት ፍርድ በድብቅ ፈርደውበታል።
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ማዕከላዊ፦ ከድብደባ​ ወደ ማባበል፥ ማታለልና ማስፈራራት! ፍትህ ለውቤ እና አይዳ

መደበኛ የወንጀል ምርመራ ዘዴ በእውነትና ዕውቀት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የስቃይ ምርመራ (Torture) ደግሞ በጉልበትና ፍርሃት ላይ የተመሠረተ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ነው፡፡ በማዕከላዊ እስር ቤት የሚገኙ መርማሪዎች ለብዙ አመታት በተጠርጣሪ እስረኞች ላይ ስቃይና ድብደባ የፈፀሙት ከእውነትና ዕውቀት ይልቅ በጉልበትና ፍርሃት ስለሚያምኑ መሆኑ እርግጥ ነው፡፡ እነዚህ መርማሪዎች የስቃይ ምርመራ እንዳይፈፅሙ ተከልክለዋል፡፡ ነገር ግን፣ የካበቱት የሥራ በጉልበትና ፍርሃት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የስቃይ ምርመራ ስለተከለከለ መርማሪዎቹ ሳይንሳዊ የምርመራ ዘዴ ተግባራዊ ያደርጋሉ ማለት አይደለም፡፡ ሰዎችን በማሰቃየት የተካኑ ሰዎች በአንድ ግዜ ተነስተው በእውነትና በዕውቀት የሚመሩ ሊሆኑ አይችሉም፡፡ ከዚያ ይልቅ ከድብደባና ማስፈራራት ወደ ማባበልና ማታለል ይሸጋገራሉ፡፡ ይህ በማዕከላዊ በነበረኝ ቆይታ በተግባር የታዘብኩት እውነታ ነው፡፡ የማዕከላዊ መርማሪዎች በዕውቀትና መረጃ ላይ ተመስተው ምርመራ ከማካሄድ ይልቅ ተጠርጣሪ እስረኞችን በዘዴ ማባበልና ማታለል ይጀምራሉ፡፡ ለዚህ ደግሞ የራሳቸውን የፈጠራ ድርሰት በመፃፍ ተጠርጣሪው “በምርመራ የሰጠሁት ቃል ነው” ብሎ እንዲፈርም ያባብሉታል፡፡ በመቀጠል ተጠርጣሪ እስረኛው ፍርድ ቤት ሲቀርብ በማስረጃነት የሚቀርብበትን ቃል “ከፈረምክ በነፃ ትለቀቃለህ” እያሉ በሃሰት ለማታለል ይሞክራሉ፡፡ በመጨረሻ ወደ ትክክለኛ ማንነታቸው በመመለስ በእስረኛው ላይ የስነ-ልቦና ጫና መፍጠርና በግልፅ ማስፈራራት ይጀምራሉ፡፡ ይህ ሁሉ ተጠርጣሪዎች የእነሱ ባልሆነ ቃል ላይ እንዲፈርሙ ለማድረግ ነው፡፡ በህጉ መሠረት፣ ተጠርጣሪ እስረኛው የእሱ ባልሆነ ቃል ላይ መፈረም ይቅርና ከነጭራሹ ቃሉን ያለመስጠት መብት አለው፡፡ ይህን በደል በዛሬው ዕለት የማዕከላዊ መርማሪዎች በመ/አለቃ አይዳ አሌሮ ላይ ፈፅመውታል፡፡ ውቤ እና አይዳ መ/አለቃ አይዳ አሌሮ በብላቴ ወታደራዊ ማሰልጠኛ የአይር
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በቂሊንጦ ቃጠሎ ሰበብ የተከሰሱት ዛሬ በችሎቱ በተፈጠረ ችግር በተከሳሾቹ ላይ ጥይት ተቀባበለባቸው

እናቶችና ሴቶች መሬት ላይ እየተንከባለሉ አለቀሱ እየተጎተቱ ከአዳራሹ ወጡ፡፡ እስረኛው እና ቤተሠብ ተደበደበ፡፡ አባቶች ተገፈተሩ ተረገጡ ተመናጭቀው ከአዳራሹ ወጡ፡፡ ወጣቶች በዱላና በቡጢ ተደበደቡ፡፡ ተከሳሾች መሳሪያ ተቀባብሎባቸው ተቀጠቀጡ፡፡ በቂሊንጦ ቃጠሎ ሰበብ የተከሰሱት ዛሬ በችሎቱ በተፈጠረ ችግር በርካታ አፈሙዝ ዞሮባቸዋል። በተከሳሾቹ ላይ ጥይት ሲቀባበልባቸው፣ አፈሙዝ ሲዞርባቸው ያዩ የተከሳሾች ቤተሰቦች ዋይታ አሰምተዋል። አልቅሰዋል። አንዲት ዮናታን ተስፋዬ ሲያፅናናቸው የነበሩ እናት “እኔ ልቅደም፣ እኔን ቀድሞ ይግደለኝ” እያሉ ለተከሳሽ ልጃቸው ሲያለቅሱ ነበር። ብዙ እናቶች ሲያለቅሱ ነበር። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ በጊኤያዊነት በ4ወንጀል ባስቻለው ችሎት 16 ተከሳሾች በማስረጃነት የቀረበባቸው ቃል በማሰቃየት የተገኘ ነው በማለት ቃላቸው በማስረጃነት እንዳይቀርብባቸው ውድቅ አድርጎታል። በእነ መቶ አለቃ ማስረሻ ክስ መዝገብ የተከሰሱት 38 ተከሳሾች ብይን እየተነበበ ነው። ከቀረበባቸው 39 የአቃቤ ሕግ ምስክር መካከል እስካሁን የ6ቱ ተነብባል። የ7ኛ አቃቤ ሕግ ምስክር ቃል እየተበበ ነው። በሌላ በኩል በቃጠሎው ሰበብ ተጠርጥረው ሸዋሮቢት ከተወሰዱ በኋላ ስቃይ የደረሰባቸው የ16 ተከሳሾች ቃል በማስረጃነት እንዳይቀርብባቸው ፍርድ ቤቱ ውድቅ አድርጎታል። ተከሳሾቹ ላይ የቀረበው ምስክርነት እየተነበበ ነው። ቃላቸው ውድቅ እንዲሆን የተደረገላቸው ተከሳሾች እና የደረሰባቸው ጉዳት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮምሽን በእነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ የክስ መዝገብ በቂሊንጦ ቃጠሎ ሰበብ የተከሰሱ 16 እስረኞች ላይ በምርመራ ወቅት የደረሰባቸውን ጉዳት በሪፖርቱ አኳትቷል። በዚህም መሰረት:_ ከበደ ጨመዳ:_ ቀኝ እጅ ላይ ትንሽ ጠባሳ፣ ቀኝ እግር አውራ ጣት ስብራት፣ ኢብራሂም ካሚል:_ ቀኝ
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የውጭ ጉዳይ ቃል-አቀባይ በነበሩት አቶ መለሰ አለም የተደበደበው ተከሳሽ ለዳኞች ቅጥረኝነታቸውን ነገራቸው።

* ስነስርአት አድርግ ዳኛ ተከሳሽን * “አንተ ስነሰርአት ሲኖርህ እኔም ስርአት አደርጋለሁ ቅጠረኞች እንደሆናችሁ አውቃለሁ” – ተከሳሽ ዳኞችን  (በፍሬው ተክሌ ረቡኒ) የውጭ ጉዳይ ቃል-አቀባይ በነበሩት አቶ መለሰ አለም የተደበደበው ተከሳሽ በእነ ጌታሁን በየነ የክስ መዝገብ 3ኛ ተከሳሽ ሰይፉ አለሙ ዛሬ ፍ/ቤት የቀረበ ሲሆን መዝገቡ ተቀጥሮ የነበረው የመከላከያ ምስክር ብይን ለመስጠት ነበር ። ዳኞች ችሎት ሳይሰየሙ በችሎት ተላላኪ በኩል ሰይፉ አለሙ በማስጠራት በቢሮ በኩል ነው የምናየው ና ተብለሀል ሲባል ተከሳሽ ሰይፉ አለሙ “እኔ መዳኘት የምፈልገው በችሎት በኩል ነው አልመጣም” በማለት መላሽ ሰጥቷል ዳኞች ስላልተሟሉ ነው ስለዚህ ቀጠሮ ለመስጠት ነው የሚል ምክንያት ቢቀርብም “በቢሮ በኩል መቅርብ አልፈልግም” በማለት እምቢ ብሏል ። በመቀጠልም ዳኞች ችሎት ያስቻሉ  ሲሆን መሀል ዳኛው እንዲህ በማለት ተናግረዋል “ተከሳሽ በዋናነት በቢሮ በኪል እንዲቀርቡ ያስፈለገው ዳኞች ስላልተሟሉ ነው ካልተሟሉ ደግመሞ ችሎት መሰየም አይችሉም፤ ጓዳ ሆኖ ተደብቆ የሚሰራ ነገር የለም፤ በቢሮ ተሰራ በፕላዝማ ተሰራ በችሎት ተሰራ ያው ነው” ካሉ በሆላ የምስክሮች ቃል ስላልተገለበጠ ቀጠሮ ነው የምንሰጠው በማለት ቀጠሮ ሊሰጡ ሲሉ ተከሳሽ ሰይፉ አለሙ “ለምንድን ነው ቀጠሮ የምትሰጡኝ? ከታሰርኩ ሁለት አመቴ ነው፤ እናንተ ቁጥር ብቻ ነው የምትጠሩት፤ ይህ የታወቀ ነው አባሪዎቼ ላይ የጠራችሁትን ቁጥር እኔም ላይ ጥሩ”  ይሄን ሲል በግራ ዳኛው በኩል በተደጋጋሚ ስነስርአት አድርግ የተባለ ሲሆን ተከሳሽም “አንተ ስነስርአት ሲኖርህ እኔ ስነስርአት አደርጋለሁ፤ ቅጥረኛ እንደሆናችሁ አውቃለሁ ፍረዱ የተባላችሁትን ነው የምትፈርዱት ጓደኞቼ
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News