Blog Archives

በቂሊንጦ እስረኞች ከትላንት ጀምሮ ለምን አንፈታም በሚል ተቃውሞ እያሰሙ ነው።

ቂሊንጦ ያሉ እስረኞች ጉዳይ አሳሳቢ ነው። የሚመለከተው አካል ደርሶ የእስረኞቹን ህይወት ሊያተርፍ ይገባል። ተመሳሳይ ስህተት ሊደገም አይገባም። ሃላፊዎቹ እስረኞቹ ላይ እንዲተኮሱ ለማረሚያ ቤት ፖሊሶች ትእዛዝ ሰጥተዋል ።የአዲስ አበባ ፖሊስ  የእስረኞች ቤተሰቦችን ደብድበዋል። ቂሊንጦ ያሉ እስረኞችን ቤተሰቦቻቸው ገብተው እንዳይጠይቋቸው ተከልክለዋል። እስረኞቹም ከትላንት ጀምሮ ለምን አንፈታም በሚል ተቃውመው እያሰሙ ነው። በአሁን ሰአት ከውስጥም ከውጪም ጩኸት እየተሰማ ነው። እስካሁን ድረስ በምን ምክንያት እንዳልተፈቱ የማይታወቅ 100 የሚሆኑ በአግ7 እና ኦነግ አባልነት ተጠርጥረው የሽብር ክስ የቀረበባቸው እስረኞች በቂሊንጦ ይገኛሉ። የማረሚያ ቤት ኃላፊዎች ተነሱ ተባለ። ቢነሱ እነ አሰፋ ኪዳነ ናቸው። የየዞኑ ኃላፊዎች የስምሪት ኃላፊዎች አብዛኛውን ቦታ የያዙት ያው ታጋዮቹ ናቸው። የመነኩሴ ልብስ ለማስወለቅ የጣሩ ብቻ ሳይሆን መነኮሳቱን መሬት ለመሬት የጎተቱ አረመኔዎች አልተነሱም። እነዚህ ለእምነት ቅንጣት ክብር የሌላቸው በእስረኞች ላይ አፈሙዝ ማዞር ሱስ ሆነባቸው። እነዚህ አረመኔዎች እስረኞችን በሚስማር ሲወጉ የነበሩ ናቸው። የጉልበት መቅኒ ለማፍሰስ በሚስማር የወጉት አለ። መሬት ላይ እያንከባለሉ ውሃ እየደፉ ሲገርፉ የነበሩ ናቸው። ራሳቸው የገደሉትን እስረኛ ለእስረኞች የሰጡ፣ የወነጀሉ ናቸው። ዝዋይና ሸዋሮቢት ቅጣት ቤት ወስደው የሰውን ልጅ ክብር በእጅጉ በሚያዋርድ ሁኔታ ያሰቃዩ፣ ሰቅለው የገረፉ፣ የሀሰት ምስክር መልምለው ያስመሰከሩ ናቸው። እነዚህ አረመኔዎች አልተነሱም። እስረኛ ይፈታ ሲባል “አብይ ያስፈታህ!” የሚሉ ቅጥ ያጡ የቀን ጅቦች ናቸው። ገድለው፣ ገርፈው አልተጠየቁም። ዛሬም ሌላ አደጋ እየፈጠሩ ነው። ዶክተር አብይ ይፈቱ ያሏቸው እስረኞች ለሕይወታቸው አስጊ ሁኔታ ውስጥ ገብተዋል! ነሃሴ 28/2008 ዓም የተፈጠረውን
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የፖለቲካ እስረኞች የርሃብ አድማ አደረጉ

የፖለቲካ እስረኞች የርሃብ አድማ አደረጉ ቂሊንጦ እስር ቤት የሚገኙ የፖለቲካ እስረኞች የርሃብ አድማ ማድረጋቸው ታውቋል። እስረኞቹ የርሃብ አድማ ያደረጉት “ግንቦት 20 ለባርነት የተዳረግንበት ቀን ነው፣ እየተሰቃየን ያለነው ግንቦት 20 ቀን ወደ ስልጣን በወጡት ነው” በሚል ምክንያት ነው ተብሏል። እስረኞቹ ከቂሊንጦ እስር ቤት የሚሰጣቸውን ምግብ “አንቀበልም” ብለው መመለሳቸውም ታውቋል። መንግስት የፖለቲካ እስረኞችን እፈታለሁ ቢልም በአሁኑ ወቅት ከ250 በላይ የክስ ሂደታቸውን በፍርድ ቤት እየተከታተሉ ያሉ እስረኞች ቂሊንጦ ውስጥ ይገኛሉ። የ”ሽብር” ክስ የተመሰረተባቸው እነዚህ እስረኞች መካከል አብዛኛዎቹ በማዕከላዊ እንዲሁም ቂሊንጦ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት የተፈፀመባቸው ናቸው።
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በቂሊንጦ እስር ቤት እና በፖለቲካ እስረኞች መካከል ውጥረት ነግሷል

ዛሬ ግንቦት 2/2010 ዓም ከሁሉም የእስር ቤቱ ማማዎች መሳርያዎች ወደ እስረኛው ተጠምደው እንዳረፈዱ ለማወቅ ተችሏል ሚያዝያ 30/2010 ዓም ቀጠሮ የነበራቸው በእነ መቶ አለቃ ማስረሻ ክስ መዝገብ 38ቱ ተከሳሾች ችሎት ከተረበሸ በኋላ ቂሊንጦ ዞን 5 የታሰሩት ተከሳሾች ድብደባ ተፈፅሞባቸዋል ከ38 ተከሳሾች መካከል 11ተከሳሾች ከፍርድ ቤት እንደተመለሱ ጨለማ ቤት ገብተዋል። ፍፁም ጌታቸውን ጨምሮ ፍርድ ቤት ላይ ጥያቄ ያነሱት ተደብድበዋል። የአጥፉ አበራ እጅ ጉዳት ደርሶበት በፋሻ እንደተጠቀለለ ታውቋል የቂሊንጦ እስር ቤት ከ38ቱ ተከሳሾች መካከል ነፃ ከተባሉት 8 እስረኞች ውጭ ሌሎቹን ዛሬ ግንቦት 2/2010 ዓም ወደ ዝዋይ እጭናለሁ በማለቱ የዞን 1 እስረኞች “ወደ ዝዋይ አይሄዱም” ብለው በመቃወማቸው ውጥረት ነግሶ እንዳረፈደ ለማወቅ ተችሏል። በዚህም መሰረት ከሁሉም የእስር ቤቱ ማማዎች ወደ እስረኛው መሳርያ ተጠምዶ አርፍዷል። የቤተሰብ ጥየቃም ተከልክሎ የነበር ሲሆን የጀመረው ከጠዋቱ አራት ሰዓት በኋላ ነው። የ38ቱ ተከሳሽ እስረኞች ከፍርድ ቤት ከተመለሱ በኋላ የርሃብ አድማ እንዳደረጉ ተገልፆአል። እስካሁንም ምግብ አልበሉም። የቂሊንጦ እስር ቤት ከአሁን ቀደምም 22 ተከሳሾችን ወደ ዝዋይ በመውሰድ ጠዋት ጠዋት ራቁታቸውን አሸዋ ላይ አስተኝቶ፣ ላያቸው ላይ ውሃ በመድፋት የግርፋትና ማሰቃየት ተግባር እንደፈፀመባቸው በችሎት መናገራቸው ይታወሳል። እስር ቤቱ ተከሳሾች ወደ ዝዋይ እጭናለሁ ሲል አለመግባባት የተፈጠረውም ከአሁን ቀደን በእስረኞች ላይ ከተፈፀመው የማሰቃየት ተግባር አንፃር ነው ተብሏል። የቂሊንጦ እስር ቤት ባልታወቀ ምክንያት ከተለያዩ የእስር ቤቱ ዞኖች ታስረው የነበሩ የፖለቲካ እስረኞችን ወደ ዞን አንድ እንዳዛወራቸው ታውቋል። በአሁኑ ወቅት
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

በቂሊንጦ ቃጠሎ ሰበብ የተከሰሱት ዛሬ በችሎቱ በተፈጠረ ችግር በተከሳሾቹ ላይ ጥይት ተቀባበለባቸው

እናቶችና ሴቶች መሬት ላይ እየተንከባለሉ አለቀሱ እየተጎተቱ ከአዳራሹ ወጡ፡፡ እስረኛው እና ቤተሠብ ተደበደበ፡፡ አባቶች ተገፈተሩ ተረገጡ ተመናጭቀው ከአዳራሹ ወጡ፡፡ ወጣቶች በዱላና በቡጢ ተደበደቡ፡፡ ተከሳሾች መሳሪያ ተቀባብሎባቸው ተቀጠቀጡ፡፡ በቂሊንጦ ቃጠሎ ሰበብ የተከሰሱት ዛሬ በችሎቱ በተፈጠረ ችግር በርካታ አፈሙዝ ዞሮባቸዋል። በተከሳሾቹ ላይ ጥይት ሲቀባበልባቸው፣ አፈሙዝ ሲዞርባቸው ያዩ የተከሳሾች ቤተሰቦች ዋይታ አሰምተዋል። አልቅሰዋል። አንዲት ዮናታን ተስፋዬ ሲያፅናናቸው የነበሩ እናት “እኔ ልቅደም፣ እኔን ቀድሞ ይግደለኝ” እያሉ ለተከሳሽ ልጃቸው ሲያለቅሱ ነበር። ብዙ እናቶች ሲያለቅሱ ነበር። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ በጊኤያዊነት በ4ወንጀል ባስቻለው ችሎት 16 ተከሳሾች በማስረጃነት የቀረበባቸው ቃል በማሰቃየት የተገኘ ነው በማለት ቃላቸው በማስረጃነት እንዳይቀርብባቸው ውድቅ አድርጎታል። በእነ መቶ አለቃ ማስረሻ ክስ መዝገብ የተከሰሱት 38 ተከሳሾች ብይን እየተነበበ ነው። ከቀረበባቸው 39 የአቃቤ ሕግ ምስክር መካከል እስካሁን የ6ቱ ተነብባል። የ7ኛ አቃቤ ሕግ ምስክር ቃል እየተበበ ነው። በሌላ በኩል በቃጠሎው ሰበብ ተጠርጥረው ሸዋሮቢት ከተወሰዱ በኋላ ስቃይ የደረሰባቸው የ16 ተከሳሾች ቃል በማስረጃነት እንዳይቀርብባቸው ፍርድ ቤቱ ውድቅ አድርጎታል። ተከሳሾቹ ላይ የቀረበው ምስክርነት እየተነበበ ነው። ቃላቸው ውድቅ እንዲሆን የተደረገላቸው ተከሳሾች እና የደረሰባቸው ጉዳት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮምሽን በእነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ የክስ መዝገብ በቂሊንጦ ቃጠሎ ሰበብ የተከሰሱ 16 እስረኞች ላይ በምርመራ ወቅት የደረሰባቸውን ጉዳት በሪፖርቱ አኳትቷል። በዚህም መሰረት:_ ከበደ ጨመዳ:_ ቀኝ እጅ ላይ ትንሽ ጠባሳ፣ ቀኝ እግር አውራ ጣት ስብራት፣ ኢብራሂም ካሚል:_ ቀኝ
Tagged with: , , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News