Blog Archives

በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያን የተጀመሩ የለውጥ ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ ትብብራቸው ተጠየቀ ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የ2011 በጀት ዓመትን አስመልክተው ከፓርላማ አባላት የቀረቡላቸውን ጥያቄዎች ከመለሱ በኃላ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያን የተጀመሩ የለውጥ ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ ሊኖራቸው የሚገባውን ሚና አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት ፍሬ ሀሳብ ፡ • ዲያስፖራ ኢትዮጵያዊ ሁሉ የሚልከውን ገንዘብ በባንክ በኩል በማድረግ የመንግስትን የለውጥ እንቅስቃሴ ደግፉ፡ • ዲያስፖራዎች ከቀን ወጨያቸው አንድ ዶላር በመለገስ በገጠር አካባቢ ያለውን ህዝብ ችግሮች መቅረፍ የሚያስችል ድጋፍ እንዲያደርግልን እለምናለሁ፡፡ • ይህን የሚያንቀሳቅስ ቦርድ ሽራፊ ሳንቲም ሳትባክን ለታሰበለት አላማ እንዲውል ይደረጋል፡፡ • ሙህራን ልምድና ክህሎታችሁን በበጎፈቃድ መልክ እያበረከታችሁ አግዙን • ወጣቶች የበጎ ፈቃድ ባህልን በማዳበር ተጨማሪ የበጀት አቅም ሁኑን • ባለሃብቶች ታክስ በመክፈል ግዴታችሁን ከመወጣት ባሻገር የሞራል ልዕልናችሁን ጠብቃችሁ የአገር አለኝታ ልትሆኑ ይገባል፡፡ • የመንግስት ሹሞች የተጣለባችሁን ኃላፊነት በአግባቡ እንድትወጡ የሚሉና ሌሎች ተማፅኖ አዘል የአብረን እንስራ ጥሪን አስተላልፈዋል፡፡
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News