Blog Archives

የልዩ ሃይሉ ፍርሰትና የአማራ ብሄራዊ ጦር ግንባታ – (ጌጥዬ ያለው)

በርግጥ የመሳፍንት ስርዓት በራሱ ከሥልጣን ሽኩቻ የዘለለ ክፋት አልነበረውም። የውጭ ወራሪ ሲመጣ የውስጥ ልዩነቱን ትቶ ጠላትን የሚያደባይ ክንደ ብርቱ ነበር። ዘመነ መሳፍንት እንደ ዛሬው ዘመነ ወራሪያን ኢትዮጵያን የሚበትን ብሄራዊ ስጋት አልነበረም። ሆኖም የኢትዮጵያ በአንድ ማዕከላዊ አስተዳድር ስር መሆን ሸጋነቱ አያጠያይቅም። ስለዚህ ስለ ላቀው የኢትዮጵያ አንድነት፣ ስለ ዘመናዊት ኢትዮጵያ ካሣ ኃይሉ ጫካ ገባ፤ ታገለ። ታዲያ መይሰው ካሣ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጦር ሲገነባ ዳገት የሆነበት በመሳፍት ክፍፍል የተያዘው ሰራዊት ነበር። ሆኖም ጀግንነቱ፣ ቆራጥነቱ እና ሞት አይፌነቱ ሁሉንም ድል እያደረገ ርዕዩን እውን ለማድረግ አስቻለው። በመሳፍንት የተከፋፈለች ኢትዮጵያንም አንድ አደረጋት። የዚህ ወቅት የአማራ ትግልም በሕዝቡ ላይ የታወጀበትን የዘር ፍጅት አስቁሞ ህልውናውን ለማስቀጠል፣ በብሄር የተከፋፈለች ኢትዮጵያን ወደ ቀደመ አንድነቷ ለመመለስ፣ ወደ መንበረ ሥልጣን ለመውጣት የቴዎድሮስን መንገድ መከተል አለበት። ለዚህም ሰሞነኛው የአማራ ልዩ ሃይል እንቅስቃሴ አጋዥ ነው። ዘመነ ወራሪያን ኢትዮጵያን በብሄር ሰነጣጥቆ እየበተናት ይገኛል። ለመበተን የቆመቺበትን ምሰሶ መንቀል ማለትም አማራን ማጥፋት ደግሞ የሁሉም ወራሪዎች የጋራ ቀዳሚ አጀንዳ ነው። ለዚህም አማራውን ያለ ተከላካይ ለመደለቅና ለማጥፋት የአማራ ልዩ ፖሊስን ትጥቅ ማስፈታት ብሎም ከነአካቴው መበተን አስፈላጊ ሆኗል። ይህንን ተቀብሎ የጠላትን ትዕዛዝ መፈፀም ለአማራው ራስን ጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ እንደመወርወር ይቆጠራል። ምርጫው ሁለት ነው፤ ወደ ገደሉ መግባት ወይም ወደ ተራራው መውጣት። ወደ ተራራው ለመውጣት አሻፈረኝ ማለትና የአማራን ብሄራዊ ጦር ግንባታ ማጠናከር ተገቢ ነው። እያንዳዱ የአማራ ልዩ ሃይል አባል የያዘውን ጠመንጃ ለአፍታም ቢሆን
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ዴሞክራሲ ብቻ! — ብርሃኑ አበጋዝ

ዶ/ር ብርሃኑ አበጋዝ – አዲስ አበባ *** በኢትዮጵያችን ዴሞክራሲን የግድ የሚያደርገውም የዴሞክራሲ (የዴሞክራሲ ሽግግር) አንቅፋቱም ዘውጌ ብሔርተኝነት ነው፡፡ ሆኖም የኢትዮጵያ መድኀን ዴሞክራሲ ነውና መንገዱ አስቸጋሪም ቢሆን በዚኸው አቅጣጫ ከመግፋት ውጪ ሌላ አማራጭ የለም፡፡ ሁሉም እንደሚያውቀው በአገራችን ላለፉት ከአርባ በላይ ዓመታት ሲቀነቀን የኖረው የዘውግ ፖለቲካ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምኅዳር ውስጥ ማዕከላዊ ቦታ ከመያዙም በላይ፣ ሌላ የፖለቲካ ትርክት የጠፋ ይመስል ሁሉም ነገር ዘውግ ተኮር ሊሆን በቅቷል፡፡ ዘውገኝነት በፖለቲካው አካባቢ ሳይወሰን የግል ዘርፉንም በክሎታል፡፡ የሠራተኛ ቅጥሩ፣ የሸር ካምፓኒ ምሥረታው፣ የኢንቨስትመንት ቦታ መረጣው ወዘተ. ሁሉ ዘውግ ተኮር ሆኗል፡፡ ይህን ነባራዊ ሐቅ ሊያስተናግድና በሒደት መልክ እንዲይዝ ሊያደርግ የሚችለው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ብቻ ነው፡፡ የኢዴሞክራሲ አማራጭ (አማራጭ ከተባለ) ወደ ምስቀልቅል ብቻ ነው ሊወስደን የሚችለው፡፡ ከዚህ በኋላ በልማታዊ መንግሥት ወይም በሌላ ‹ኢ-ሊብራል› አማራጭ እያሳበቡ የኢኮኖሚ ልማት እስኪረጋገጥ ድረስ በኢዴሞክራሲያዊ መንገድ ማዝገም ይቻላል ማለት ፈጽሞ ጊዜው አልፎበታል፡፡ “መደመር” የሚለው የነ ዶ/ር ዐቢይ መርህ ከዚህ የተለየ ስለመሆን አለመሆኑ ወደፊት የሚታይ ይሆናል፡፡ ኢትዮጵያዊያን እየወደቅንም እየተነሳንም፣ እያጠፋንም እያለማንም ቢሆን ዴሞክራሲን ብቻ ነው መለማመድ ያለብን፡፡ ወጣቱ፣ ዘውጌ ብሔርተኝነትና ዴሞክራሲ *** በግልጽ እንደሚታየው የለውጡ እንቅስቃሴ ሞተሩ ወጣቱ ነው፡፡ ይኽ በገጠርም በከተማም የሚኖር ወጣት የኅብረተሰብ ክፍል ደግሞ 70 ከመቶ የኅብረተሰብ ክፍል ድርሻ አለው፡፡ ወጣቱ ነገሮች ቢመቻቹለት በአጭር ጊዜ ወደ መካከለኛ መደብ ሊደርስ የሚችል ኀይል ነው፡፡ ነገሮች ቢመቻቹለት፣ ትክክለኛ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ቢቀየስለት፣ ትክክለኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ቢዘረጋለት በአጭር
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ዴሞክራሲ፤ እንዴት? ( አሸናፊ ሞላ )

ዴሞክራሲ፤ እንዴት? *** አሸናፊ ሞላ *** በአገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ተፈቅዷል ከተባለበት ከ1984 ዓ.ም. ጊዜ ጀምሮ በርካታ የፖለቲካ ድርጅቶች ተቋቁመዋል፤ ከተቋቋሙት ድርጅቶች መካከል በርካቶች ይህ ነው የሚባል ተግባር ሳይፈፅሙ፣ ሕዝብም ከነመኖራቸው ሳያውቃቸው ሞተዋል፤ የቀሩት በየጊዜው እየተሰነጣጠቁ በከፍተኛ ደረጃ ተዳክመዋል፡፡ ይኹን እንጂ አሁንም አዳዲስ የፖለቲካ ድርጅቶች እየተቋቋሙ ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ አሁን ከምንገኝበት እጅግ አሳሳቢ ሁኔታ እንድንወጣ እና የሰለጠነ የፖለቲካ ባህል እንድንገነባ ካስፈለገ በተለመደውና በኖርንበት መንገድ መቀጠል እንደማንችል፤ የሚያስፈልገን ከላይ ከማዕከል ወደታች የሚንቆረቆር ሳይሆን ከታች ወደላይ እየተገነባ የሚሄድ የፖለቲካ ዘይቤ እንደሆነ፣ ይህን ለማድረግ የሚያስችለን አደረጃጀት ደግሞ ፓርቲ ሳይሆን ንቅናቄ ስለመሆኑ ለማብራራት እሞክራለሁ፡፡ በጽሑፉ የመጀመሪያ ክፍል የፖለቲካ ፓርቲና የንቅናቄን ምንነት በአጭሩ ካስታወስኩ በኋላ፣ ለጠቅ አድርጌ ለምን ንቅናቄ እንደሚያስፈልገን እና ንቅናቄዎቹ በምን መልኩ ሊደራጁ እንደሚችሉ (እንደሚገባ) የተወሰኑ ነጥቦችን እሰነዝራለሁ፡፡ የፖለቲካ ፓርቲንና የንቅናቄን ልዩነትና ተመሳሳይነት በሚመለከት አንድ ሁሉን የሚስማማ ብያኔ መስጠት ባይቻልም፣ ለዚህ ጽሑፍ ሲባል “የፖለቲካ ፓርቲ ለፖለቲካ ሥልጣን የሚታገል፣ በሕግ የተመዘገበ እና ከሞላ ጎደል ተቀራራቢ የፖለቲካ አስተሳሰብና ዓላማ ያላቸው ዜጎች ስብስብ ነው፤” የሚለውን ብያኔ እንደመነሻ እንጠቀም፡፡ ማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ ለፖለቲካ ሥልጣን ከመወዳደሩ በፊት ይብዛም ይነስም የራሱ የሆነ፣ ብመረጥ አስፈጽመዋለሁ የሚለው ፕሮግራም ይኖረዋል፡፡ ፓርቲው ይህን የፖለቲካ ፕሮግራሙን ለሕዝብ በማስተዋወቅና ሕዝብ እንዲቀበለው በማድረግ፣ ይልቁንም ከሌሎች ተቀናቃኝ ፓርቲዎች ጋር ሲወዳደር የእሱ ፕሮግራም የተሻለ እንደሆነ በማሳመን ለፖለቲካ ሥልጣን ይታገላል፡፡ አብላጫ ድምጽ አግኝቶ የመንግሥት ሥልጣን ከተረከበም ያቀረባቸውን የፖሊሲ አጀንዳዎች
Tagged with: , ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

የዴሞክራሲ ሽግግር እንቅፋቶች – መሐመድ አሊ (ዶ/ር)

የዴሞክራሲ ሽግግር እንቅፋቶች *** መሐመድ አሊ (ዶ/ር) *** የዴሞክራሲ ሽግግር (democratization) ከፍ ያለ አባጣ ጎርባጣ ያለበት ጉዞ ነው፡፡ ጉዞው እንደሁኔታዎች አስገዳጅነት አንድ እርምጃ ወደፊት ኹለት እርምጃ ወደኋላ ሊሆን ይችላል፡፡ በሒደቱ ውስጥ በርካታ ተዋናዮች ስላሉ፣ እነኝህ ተዋናዮች በሽግግሩ ላይ በአወንታዊም ይሁን በአሉታዊ መንገድ ተጽዕኖ ያሳድሩበታል፡፡ የአገሮች የዘውግና የሃይማኖት ስብጥር፣ የዕድገት ደረጃ እና መካከለኛ ገቢ ያለው ኅብረተሰብ መጠን፣ የሚዲያው ሙያዊ አቅምና የሥነ-ምግባር ሁኔታ፣ በፖለቲካ ልሂቃኑ መሀከል ያለው መስተጋብር ጠናማ መሆን ወይም አለመሆን ወዘተ. በሒደቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳድራሉ፡፡ ከላይ ከተጠቀሱት መሠረታዊ ጉዳዮች ውስጥ የተወሰኑትን ወስደን የአገራችንን የዴሞክራሲ ሽግግር እጣ-ፈንታ በምንፈትሽበት ጊዜ፣ መንገዳችን ፈታኝ ሊሆን እንደሚችል መረዳት ይቻላል፡፡ እንደሚታወቀው በአገራችን የፖለቲካ ልሂቃን መሀከል ከፍተኛ አለመግባባትና ክፍፍል የፈጠሩ አጀንዳዎች አሉ፡፡ የታሪክ ባለሙያዎች እንደሚነግሩን፣ ከቀደመው የኢትዮጵያ ምስጢራዊ ባህል ላይ ከ1960ዎቹ ወዲህ በአገራችን ነግሶ የቆየው ሌኒኒስትና ስታሊኒስታዊ አስተምህሮ የፖለቲካ ጥያቄዎችን በሰለጠነ መልኩ ተወያይቶና ተከራክሮ ከመፍታት ይልቅ፣ የተለየ ሐሳብ የሚያራምደውን ወገን በኀይል ጸጥ የማሰኘት፣ ጥላሸት የመቀባትና አላስፈላጊ ስም የመስጠት አካሄድን የተከተለ ነው፡፡ ይህ ኢዴሞክራሲያዊ ባህል ከአርባ ዓመታት በላይ የአገራችንን ፖለቲካ ተቆጣጥሮት ቆይቷል፤ በዚህም ምክንያት የውይይትና የክርክር ባህላችን ሳይዘምን እዚህ ደርሰናል፡፡ አንዱ፣ ምናልባትም ዋነኛው የአገራችን የዴሞክራሲ ሽግግር ደንቀራ ይህ የፖለቲካ ልሂቃኑ ኢዴሞክራሲያዊ ባህል ነው፡፡ የዴሞክራሲ ሽግግሩ የሰመረ እንዲሆን ካስፈለገ የፖለቲካ ልሂቃኑ ቆሞ-ቀርነት መሠረታዊ ሊባል በሚችል መልኩ መስተካከል አለበት፡፡ በመደብ ትግል ስም እርስ በርሱ ከተጨፋጨፈው የፖለቲካ ልሂቅ የተረፈው ራሱን
Tagged with: ,
Posted in Amharic News, Ethiopian News

ዴሞክራሲ ወይስ የአገር ህልውና? (ብርሃኑ አበጋዝ)

ዶ/ር ብርሃኑ አበጋዝ – አዲስ አበባ *** “ደኅንነት ወይስ ነጻነት? ዴሞክራሲ ወይስ የአገር ህልውና?” የሚሉት ጥያቄዎች የፖለቲካ ፍልስፍና ነባር ጥያቄዎች ናቸው፡፡ ብዙ ክርክር ተደርጎባቸዋል፤ እየተደረገባቸውም ነው፡፡ በዚህች አጭር ጽሑፍ፣ ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መስፈን እና የአገር ህልውና መጠበቅ በእኩል ደረጃ እንደሚያስፈልጉን፤ ስለሆነም ከኹለቱ መሠረታዊ አጀንዳዎች አንዱን መምረጥ እንደሌለብን ለመግለጽ እሞክራለሁ፡፡ አንድ የአፈና አገዛዝ በሕዝብ ትግል ተንበርክኮ የፖለቲካ ሽግግር በሚደረግበት ጊዜ፣ በሽግግር ወቅት ግጭቶች እንደሚበረክቱ፣ የሰው ሕይወትም እንደሚጠፋ የታወቀ ጉዳይ ነው፡፡ የቀደመው አገዛዝ ቅሪቶች ለውጡን ለማደናቀፍ፣ የለውጥ ኀይሎች ለውጡን ከቅልበሳ ለመጠበቅ፣ ልዩ ልዩ የፖለቲካ ተዋናዮች ደግሞ ለውጡን በራሳቸው መንገድ ለመጋለብና የራሳቸውን ዓላማ ለማስፈጸም፣ ሁሉም በየፊናቸው ይታገላሉ፡፡ በዚህ ሒደት አገርና ሕዝብ ከፍ ያለ ያለመረጋጋት ሰለባ ይሆናሉ፡፡ ዜጎች የገደላቸው ሳይታወቅ እንደወጡ ይቀራሉ፡፡ ሁሉም ነጻነቱን ተጠቅሞ እንደፈለገ ስለሚቀሰቅስ በኅብረተሰብ መሀከል ጥርጣሬና ጥላቻ ይፈጠራል፤ ግጭቶችም ይከሰታሉ፡፡ ብዙ ጊዜ የዘር ፍጀት የሚከሰተውም እንዲህ ባለ የፖለቲካ ሁኔታ ውስጥ ነው፡፡ ግጭት ሲበረክትና አለመረጋጋት ሲሰፍን፣ ብሩህ ነገር እናገኛለን፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንመሠርታለን ብሎ የለውጡ አካልና ደጋፊ የነበረው ዜጋ፣ አገዛዙ አገር ወደ ቀውስ ከማምራቷ በፊት ሕግና ሥርዓትን እንዲያሰፍን ወደ መጠየቅ ያተኩራል፡፡ በዚህ ምክንያት መጀመሪያ ሕግና ሥርዓት ይስፈን፣ የአገር ህልውና ይጠበቅ የሚለው ነጥብ ቀዳሚ አጀንዳ ሆኖ ይወጣል፡፡ በብዙ አገሮች፣ በተለይም መሠረታዊ የፖለቲካ ለውጥ በተካሄባቸው አገሮች ውስጥ ይህ የኅብረተሰብ ጥያቄ ነው አንድ የአፈና አገዛዝ በሌላ ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ እንዲተካ ምክንያት የሚሆነው፡፡ ቅድሚያ ለኅብረተሰብ
Tagged with:
Posted in Amharic News, Ethiopian News