የኤርትራው መርሐዬ መንግሥት ኢሳያስ አፈወርቂ ባደረጉላቸው ጥሪ መሠረት ከፍተኛ የኢትዮጵያ የልኡካን ቡድን የፊታችን እሁድ አስመራ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል ።የልዑካን ቡድኑ በዶክተር አብይ የሚመራ መሆን አለመሆኑ ማስታወቂያው አይገልፅም።
በአስመራ ከተማ ለሚገኙ መምሕራን እና የመንግስት ሰራተኞች የተለጠፈው ማስታወቂያ እንዳመለከተው ” ከአዲስ አበባ የሚመጡ እንግዶች ስላሉ እሁድ ከጠዋቱ 7፡30 ተኩል ጀምራችሁ ሁላችሁም በመንግስት ተቋማት ውስጥ የምታገለግሉ በሙሉ ወደ አስመራ ትምህርት ሚኒስትር ፅ/ቤት እንድትመጡ” የሚል መልዕክት የያዘ ነው ።