#Ethiopia #AbiyAhmed #TPLF
ለዘመናት በሀገራችን የሰራ አካል ውስጥ ተሰግስጎ የኖረው ሕወሓት አለ፡፡ የህ ቡድን ራሱን እያፋፋ፣ ኢትዮጵያን በአንጀት – በደም ሥርዋ ሰርጎ ሲጣባ – ሲመርዛት ኖሯል፡፡ አሸባሪው ሕወሐት አሁን ተጠራርጎ ሊወጣ አፋፍ ደርሶና ጣዕረ ሞት ይዞት በመንፈራገጥ ላይ ይገኛል። እድሜውን ለማራዘም የመጨረሻ መፍጨርጨርና የሞት ሽረት ትግል ላይ ነው። የአልሞት ባይ አትርሱኝ መወራጨቱ በዝቷል። ከግብአተ መቃብሩ በፊት ልትወጣ ያለች ነፍሱ እስካለች ድረስ መንፈራገጡና የሰላም ደንቃራ መሆኑ አይቀርም። ክፉ መርዙን ተክሎ ጥገኝነቱን ከመሠረተበት የሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተነቅሎና ተጠራርጎ እስኪወጣ ድረስ ደዌ ነውና ሕመሙን ችለን፣ የማሻሪያ መድኃኒት እየወሰድን እንቆያለን። - ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ
- Category
- Ethiopian News