ሰይፋ ፋንታሁን ህዝቡን በይፋ ይቅርታ ጠየቀ
ጋዜጠኛ ሰይፋ ፋንታሁን የአገዛዙ ልሳን መሆን በተለያዩ ጊዜያት ህዝቡን ሲያሳዝን የነበረ ጋዜጠኛ ከአገዛዙ ስርአት ጋር በመሞዳሞድ በህዝቡ ላይ ሲያፌዝ የነበረ ጋዜጠኛ ነው በቅርቡ እንኳን የመንግስት ሚዲያዎች የከለከሉትን የህዝብ ጠላት በረከት ስምኦንን በመዝናኛ ፕሮግራሙ ማቅረቡ ይታውሳል።
በመጨረሻም ጋዜጠኛ ሰይፋ በኢቢኤስ በሚያዘጋጀው ፕሮግርሙ የ2010 የመጨረሻ ዝግጅት ላይ ጊዜው በይቅርታ የመደመር ነው ነገር ግን ህዝቡ አንዳንድ አርቲስቶችን እና ባለ ሀፍቶችን ይቅርታ አላደረገም በበኩሌ ግን ሳላውቅ በስህተት ሳውቅ በድፍረት የሰራሁትን ጥፋት ይቅር በሉኝ አፋ እንባባል ብሏል።