ሰሞኑን ደግሞ ፀጥታ አስከባሪዎች ጥያቄ ያቀረበዉን ሕዝብ አስተባብረዋል ባሏቸዉ ሰዎች ላይ እርምጃ በመዉሰዳቸዉ ግጭት ተከስቷል።በግጭቱ በርካታ ሰዎች መገደላቸዉን፤ ቤትና ንብረት መጥፋቱን የአይን ምስክሮችና ፖለቲከኞች አስታዉቀዋል…
ሰሞኑን ደግሞ ፀጥታ አስከባሪዎች ጥያቄ ያቀረበዉን ሕዝብ አስተባብረዋል ባሏቸዉ ሰዎች ላይ እርምጃ በመዉሰዳቸዉ ግጭት ተከስቷል።በግጭቱ በርካታ ሰዎች መገደላቸዉን፤ ቤትና ንብረት መጥፋቱን የአይን ምስክሮችና ፖለቲከኞች አስታዉቀዋል…
ዘንድሮ በተለያዩ ውድድሮች ስኬታማ ውጤቶችን ያስመዘገበችው የ5000 እና 10,000 ሜትር ሩጫ ብርቱ ተፎካካሪዋ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አልማዝ አያና ከሪዮ ኦሎምፒክ ድሏም በኋላ ተጨማሪ ድል አስመዝግባለች።…
ኢትዮጵያ ዉስጥ እየተካሄደ ያለዉ ግድያና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እስርና እንግልት ይቁም፤ የመንግስት የፀጥታ ኃይላት በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚወስዱትን የኃይል እርምጃ ያቁሙ፤ የታሰሩ ፖለቲከኞች የሐይማኖት መሪዎችና ጋዜጠኞች ይፈቱ፤ የዘር መድሎ ይቁም ሲሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን ዛሬ ጀርመን መዲና በርሊን ላይ የተቃዉሞ …
ብሪታንያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ለንደን በሚገኘዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፊት ለፊት ተሰልፈዉ የኢትዮጵያ መንግሥት እየፈፀመ ያለዉ ግፍ ይብቃ ሲሉ የተቃዉሞ ሰልፍ ማድረጋቸዉ ተመልክቶአል ።…
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቤቶችና የከተማ ልማት ሚኒስቴር የሥራ አፈፃፀም ዝርዝር ዘገባ ባደመጠበት ወቅት ጠፉ እየተባለ ስለሚነገርላቸዉ የኮንደሚኒየም ቤቶች የሚኒስቴር መሥርያ ቤቱ አጣርቶ እንዲያቀርብ መጠየቁ ተሰምቷል። ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ታቅደዉ ያልተሠሩ መኖራቸዉን ለምክር ቤቱ ቢጠቁምም፤ ጠፋ የተባሎት የኮንደሚኒየም ቤቶች ጉዳይ …
ነገረ ኢትዮጵያ የተሰኘዉ ጋዜጣ አዘጋጅ ጌታቸዉ ሽፈራዉ ክስ ሳይመሰረትበት ከአራት ወራት በላይ መታሠሩን ጠበቃዉ አስታወቁ። ጠበቃ አመሐ መኮንንን ዛሬ እንዳስታወቁት የሐገሪቱ የፀረ-ሽብር አዋጅ በሚያዘዉ መሠረት ፖሊስ በደንበኛቸዉ ላይ በአራት ወራት ዉስጥ ክስ መመሥረት አለያም እስረኛዉን መልቀቅ ነበረበት። ፖሊስ በተደጋጋሚ የጊዜ …
በጥቂት ቀናት ልዩነቶች ውስጥ የደረሱትን እነዚህን ጥቃቶች መንግሥት ፈጥኖ መከላከል አለመቻሉ ደግሞ እያስወቀሰው ነው ። ከግጭቱ በኋላም ስለተወሰዱ እርምጃዎች ግልፅ መረጃ ባለመስጠትም እየተተቸ ነው…
ገጣሚ ናቸዉ። ፀሐፌ ተዉነትም። ከብዙ የግጥምና የተዉኔት ድርሰቶቻቸዉ መሐል ጣልቃ የገባች አንዲት የታሪክ መፅሐፍ አለቻቸዉ። መፅሐፏ በ19ኛዉ መቶ ክፍለ-ዘመን በሥነ-ፅሑፉ መድረክ ዓለም አቀፍ ክብርና ሞገሥ ያተረፈዉ የሩሲያዊዉ ባለቅኔ የአሌክሳንደር ሰርግዬቪች ፑሽኪን ታሪክን ነዉ የምትወሳዉ።
በእሳቸዉ አገላለፅ «ሕዝባዊ» የሚሉት ለገበሬዉና ለዝቅተኛዉ …
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ የወንጀል ችሎት በሽብር ተግባር በተከሰሱ ሰባት ተከሳሾች ላይ ዛሬ ከሰባት እስከ ዘጠኝ ዓመት ፅኑ የእስራት ቅጣት በየነ። በብይኑ መሰረት፣ የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚደንት አቶ ኦኬሎ ኦኳይ …
ባለፈዉ ሐሙስ በጋምቤላ ክልል በጄዊ የስድተኞች መጠለያ ካምፕ አከባቢ ንብረትነቱ /ACF/ የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት የሆነ አንድ ተሽከርካሪ ባደረሰው አደጋ ሁለት የስደተኞች ልጆች ከሞቱ በኋላ ስደተኞቹ 21 የአካባቢውን ነዋሪዎች ሲገድሉ፣ ከ10 በላይ መቁሰለቸዉን ዘገባዎች ያሳያሉ …
«የሽምብራው ጥርጥር የዛፎቹ ፍሬ የትም የትም ዞሬ ትዝ አለኝ ሀገሬ» የዛሬ ሳምንት ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩን «የመሰንቆው ሊቅ» ጌታመሳይ አበበ ዘመን ተሻጋሪ ከሆኑ የባህል ሙዚቃ ጨዋታዎች በግንባር ቀደምትነቱ የሚታወቀዉ ነዉ። ሁለ ገቡ ከያኒ ጌታመሳይ አበበ «የጥበብ ገበሪም » በመባል ይታወቃሉ።…
ጥር 9/2008 ዓ.ም. ማለዳ ከአዲስ አበባ ወደ አዳማ አዲስ በተገነባው የፍጥነት መንገድ ላይ ይጓዝ የነበረ አሽከርካሪ መኪናውን መቆጣጠር ተስኖታል። የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪው በከፍተኛ ፍጥነት እየተጓዘ ነው። ከተቃራኒ አቅጣጫ አንድ መለስተኛ አዉቶቡስ አስራ ስድስት ሰዎች ጭኖ ከአዳማ ወደ አዲስ አበባ እየተጓዘ …
የዓለም የጤና ድርጅት ሰነድ እንደሚለዉ በአሁኑ ወቅት የዓለማችን 37 ሚሊየን ሕዝብ HIV ተሐዋሲ በደሙ ዉስጥ ይገኛል። ባለፈዉ ጎርጎሪዮሳዊ ዓመት 2015 ላይ 16 ሚሊየኑ ፀረ ኤች አይቪ መድኃኒት እንደሚወስዱ ተመዝግቧል። በሽታዉ እስካሁን ከ34 ሚሊየን በላይ ሰዎችን ሕይወት ቀጥፏል። የመድኃኒቱ ስርጭት እና …
በተለያዩ ምክንያቶች ከአፍንጫ ደም ሊፈስ ይችላል። ነስር የምንለዉ ማለት ነዉ። ብዙዎች መንስኤዉ ምንድነዉ ብለዉ ይጨነቃሉ። ነስር ድንገተኛ እና አስደንጋጭ የመሆኑን ያህል አብዛኛዉን ጊዜ ቤት ዉስጥ ሊቆጣጠሩት የሚቻል እንደሆነ አንዳንድ የህክምና ጽሑፎች ይጠቁማሉ። ሆኖም አልፎ አልፎ ደግሞ ብዙ ደም የሚፈስበት ከባድ …
በምዕራብ ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ድንበር የተሻገሩ ታጣቂዎች በዕለተ አርብ ማለዳ በፈጸሙት ጥቃት ህጻናት መታገታቸውን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል-አቀባይ ተናገሩ። ቃል-አቀባዩ አቶ ተወልደ ሙሉጌታ በጥቃቱ ምን ያኽል ሰዎች ታግተው እንደተወሰዱ አለመናገራቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
በትንሹ 140 ኢትዮጵያውያን በተገደሉበት ጥቃት …
ጋምቤላ ኢትዮጵያ ውስጥ ከ140 በላይ ሰዎች ዐርብ ሚያዝያ 7 ቀን፣ 2008 ዓ.ም. ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች ተገደሉ። የኑዌር ጎሳ አባላት የመኖሪያ መንደሮች ላይ ባነጣጠረው ጥቃት የተገደሉት ሰዎች ቁጥር ከ221 በላይ መሆኑን ሱዳን ትሪቡዩን ዘግቧል …
ጫት ለኢትዮጵያ የሚሰጠው ጥቅምና በጤና ላይ የሚያስከትለው ጉዳት በቅጡ እንዲጤን ስለ ጫት ጥናታዊ ጽሁፎች ያቀረቡ ምሁራን አሳሰቡ ። «ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ» የተባለው መንግሥታዊ ያልሆነው ድርጅት ባዘጋጀው አዲስ አበባ ውስጥ ለሁለት ቀናት በተካሄደው ዐውደ ጥናት ላይ የጫት ኤኮኖሚያዊ እና ባህላዊ …
የአፍሪቃ ኅብረት ርዕሰ መዲና አዲስ አበባ በርካታ ዲፕሎማቶችን የምታስተናግድ ብትሆንም የመብራት ኃይልን ጨምሮ የዉኃ አቅርቦት እጥረት ችግር ላይ መዉደቅዋን አስመልክቶ የተለያዩ ዘገባዎች እየወጡ ነዉ።
የከተማዋ ነዋሪዎች በተለይ በቅርቡ ለዉኃ እጥረት የመዳረጋቸዉ መንስኤ ምንድነዉ ብለን አዲስ አበባ የዉኃና ፈሳሽ ባለስልጣን ምክትል …
ለሟቹ ኢትዮጵያዊ ዕዉቅ ሠዓሊ ለሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ መታሰቢያ የተሠራዉ ሐዉልት ባለፈዉ ሳምንት ማብቂያ ተመርቋል። ዓለም አቀፍ አዉቅና ያተረፉት እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ያረፉት ከዓራት ዓመት በፊት ነበር። አዲስ አበባ ዉስጥ በመንበረ ፅባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል …
ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓጓዘው የእርዳታ እህል እና ማዳበሪያ ጭነት መብዛት በአገሪቱ የትራንስፖርት ዋጋ ንረት ፈጥሯል። የኢትዮጵያ መንግስት ጅቡቲ ወደብ ላይ የተፈጠረውን መጨናነቅ ለመቀነስ የበርበራ ወደብን ለመጠቀም ስምምነት ፈርሟል። ለመሆኑ የሶማሌላንድ የበርበራ ወደብ ምን ያክል ለአጠቃቀም ምቹ ነው?
የኢትዮጵያ መንግስት ከዚህ …
የኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት ሰጭ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ሰሞኑን በቫይበር፣ በዋትስ አፕና መሰል የድምፅ ጥሪ አገልግሎቶች መስጫዎች ላይ ክፍያ ለመጠየቅ እንዳቀደ የኩባንያዉ የሥራ አመራር ለተለያዩ ሚዲያዎች መናገራቸዉ ይታወቃል።
በእነዚህ የቴክኖሎጂ ዉጤቶች ላይ ክፍያ ለመጣል የታሰበበት ምክንያት፤ መንግስት ማገኘት የሚችለዉን ከፍተኛ ገቢ ሳያገኝ …
የኢትዮጵያ መንግስት ለመሰረተ-ልማት ግንባታዎች ከቻይና ብቻ 17.6 ቢሊዮን ዶላር ተበድሯል። የኢትዮጵያ መንግስት ለሰፋፊ የመሰረተ-ልማት ግንባታዎች እና የማምረቻ ዘርፉን ለማሳደግ ከውጭ አገራት የሚበደረው ገንዘብ መጠን ያሰጋቸው ባለሙያዎች ግን ከአመት አመት በሚጨምረው ብድር ምክንያት አገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ያሰጋታል እያሉ ነው …
አዋሳኝ ድንበራቸዉም የጦር ሐይል ፍጥጫ፤ ጠብ እና ቁርቁስ ተለይቶት አያዉቅም። አሁን በሰዎች መታገት በተለይ የኢትዮጵያን የምጣኔ ሐብት እና የሰዉ ሐይል ዋና ዋና ማዕከል ኦሮሚያን በሚንጠዉ ተቃዉሞና አመፅ ሰበብ እንዳዲስ መቀጣጠሉ «የከፋ ይከተላል» የሚል ሥጋት ማጫሩ አልቀረም-እንደ ሮንግ …