በመጪው ግንቦት ወር መጨረሻ ለሚካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ በርካታ ዕጩዎችን ካስመዘገቡ ፓርቲዎች ተርታ አንድ እምብዛም ስሙ የማይሰማ ፓርቲ መገኘቱ ከሰሞኑ መነጋገሪያ ሆኗል። “እናት” የሚል መጠሪያ ያለው ይህ ሀገር አቀፍ ፓርቲ የእውቅና ሰርተፍኬት ባገኘ በአንድ ወር ውስጥ “እንዴት በርካታ ዕጩዎችን ማስመዝገብ ቻለ? አባላቶቹስ እነማን ናቸው? ” ስንል የፓርቲውን ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሰይፈሥላሴ አያሌውን ጠይቀናል።
ምክትል ፕሬዝዳንቱ ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ለቀረበላቸው፤ “ፓርቲው የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አደረጃጀቶችን ተጠቅሟልን?” ለሚለው ጥያቄም ምላሽ ሰጥተዋል። ፓርቲያቸው በሚወዳደርባቸው ቦታዎች ድምጽ ካገኘ፤ ገዢውን ፓርቲ ጨምሮ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር የጥምር መንግስት በመመስረት ጉዳይ ላይ ያለውን አቋምም አብራርተዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
- Category
- Ethiopian News