የትግራይ ሰራዊት ዋና ኣዛዥ ታጋይ ታደሰ ወረደ (ወዲ ወረደ) በወቅታዊ ጉዳይና ስኔ 21 አስመልክቶ የሰጡት መግለጫ
የትግሬ ወራሪ በታደሰ ወረደ በኩል ጦርነቱ አይቀሬ መሆኑን ተናግሯል። ለጦርነቱ የሚያበቃቸውን ሁሉንም ዝግጅት እንደጨረሱ በትግርኛ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል። ለአይቀሬው መዘጋጀታቸውን ገልፆአል። ከዚህ ጊዜ በኋላ ከእስካሁኑ የተለየ ጦርነት እናደርጋለን፣ ይህ ጦርነት የመጨረሻ አላማችን ማስፈፀሚያ ይሆናል ብሏል። ለአገር ምስረታው መሆኑ ነው። ሕዝብ መቸ ትጀምራላችሁ፣ ለምን አታጠቁም እያለ እየወተወተን ነው ያለው ታደሰ ወረደ ግድ የላችሁም አታጣድፉን እናሳያችኋለን አይነት መልዕክት አስተላልፏል።
ሰራዊታችን የትኛውንም አካል ያጠቃል ብሏል። ድርድሩ ድሮም የትግሬ ወራሪ የጊዜ መግዥያ ስልት ነው። የትግሬ ወራሪ ከአሁን ቀደሙ የከፋ ጦርነት እንደሚያደርግ እየገለፀ መዘናጋቱ ዋጋ ያስከፍላል። በፈለግነው ሰዓትና ጊዜ ጦርነት እንከፍታለን ብሏል። ለከፋው መዘጋጀቱ የተሻለ ነው።
- Category
- Ethiopian News