አሁንም ለወገን ደራሽነታቸውን ያሳዩበት
ድምጻዊ አለማየሁ እሸቴ "ተማር ልጄ" የተሰኘው ዜማ በድጋሚ ከሮሃ ባንድ ጋር በመሆን አቀንቅኖታል። ይህ ዜማ እንደ ቀድሞ አባት ልጁን እንዲማር አይመክርም፤ ይልቅስ አባት ለልጁ ራሱን ከኮሮናቫይረስ እንዲጠብቅ የሚያስታውስ ነው።
ከአለማየሁ እሸቴ ጋር ድምፃዊ ሞገስ መብርሃቱ እና ድምጻዊት አስቴር ከበደ ያቀነቀነች ሲሆን ግጥሙን የፃፈው ደግሞ አበረ አዳሙ ነው።
ልክ እንደሰው ታሞ ኮስምኗል ዘመኑ
በደስታችን ዙፋን ተሾሟል ሐዘኑ
ከቤትህ ተሰብሰብ በመምሸቱ አትስጋ
ነገም ብርሃን አለ ጨለማው ሲነጋ. . . ይላል ድምጻዊ አለማየሁ እሸቴ።
- Category
- Ethiopian News Ethiopian Music