#Ethiopia #AmharaGenocide
ዛሬ መደበኛ ስብሰባውን ሊያደርግ የተሰበሰበው ፓርላማ በጉሊሶ ወረዳ በተፈፀመው ጥቃት ዙሪያ ረጅም ሰዓት ወስዶ ተነጋግሯል።
አባላት በእንባ የታጀበ ከፍተኛ ቁጣቸውንም ገልፀዋል፡፡
ስራ አስፈጻሚው አካል ቀርቦ ማብራሪያ እንዲሰጥና ቀጣይ እርምጃውን እንዲያሳውቅ ምክር ቤቱ ወስኗል።
"አንድ ሰራዊት ከአንድ ቦታ ሲነሳ በፊት ስጋት አለበት ተብሎ ያ ስጋት የለም ተብሎ የሚኒሳ ከሆነ በአካባቢው የሚገኝ ታጣቂ ያንን ቦታ እንዲቆጣጠረው የመረካከብ ስነ ስርዓት መደረግ ነበረበት።
ይሄ ሳይደረግ መቅረቱ ለምንድ ነው ? የሚለውን መከላከያ ሰራዊትም አጠቃላይ መንግስት ይህን ጉዳይ ለምን እንደዚህ አይነት ክፍተት ሊከሰት ቻለ የሚለውን ተገምግሞ ለምክር ቤቱ ሊቀርብለት ይገባል።"
- Category
- Ethiopian News