Loading...

ከግብፅ ጋር የሚደረገውን ድርድር በበላይነት የሚመራ "ብሔራዊ ኮሚቴ" ሊቋቋም ይገባል!

Thanks! Share it with your friends!

You disliked this video. Thanks for the feedback!

Added by addis

የህዳሴው ጎድብ ግንባታ ከተጀመረ በኋላ ግብፆች የአባይ ጉዳይ በሀገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት ስር እንዲሆን አድርገዋል። የኢትዮጵያና ሱዳን የውሃ ሚኒስትሮች ከግብፆች ጋር በሚያደርጉት ድርድር ውሳኔ የሚሰጠው የግብፅ ውሃ ሚኒስቴር ሳይሆን የግብፅ ደህንነት ሃላፊ ነው። ስለዚህ ግብፆች በአባይ ላይ የሚያደርጉት ድርድር የውሃ ጉዳይ መሆኑ ቀርቶ የብሔራዊ ደህንነት ጉዳይ ከሆነ ሰንብቷል። የኢትዮጵያን የውሃ ሚኒስትር ከግብፅ የደህንነት ሃላፊ ጋር እንዲደራደር ማድረግ ተገቢ አይደለም። ከዚያ ይልቅ የአባይና የህዳሴውን ግድብ የተመለከቱ ስራዎችን የሚሰራ ብሔራዊ ኮሚቴ ሊቋቋም ይገባል። በተለይ በውሃና ኢነርጂ፣ በውጪ ጉዳይ እና በመረጃና ደህንነት መስሪያቤቶች ውስጥ በአባይ ድርድር ዙሪያ ላይ የሚሰሩ የሥራ ክፍሎች (ዴስኮች) ሊቋቋሙ ይገባል። እነዚህን የስራ ክፍሎች በበላይነት የሚመራ በሚኒስቴሮች ደረጃ ብሔራዊ ኮሚቴ መዋቀር አለበት።
***

Category
Ethiopian News

Post your comment