የሰሜን ሸዋ ዞን የክተት ጥሪ
አማጺው ሕወሃት እና የኦሮሞ ነጻ አውጭ ሠራዊት ጋር በቅንጅት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ላይ መጠነ ሰፊ ወረራ መፈጸማቸውን የዞኑ አስተዳደር ዛሬ በማኅበራዊ ትስስር ገጾቹ ባሠራጨው መግለጫ አስታውቋል። ሁለቱ ቡድኖች በዞኑ በይፋት እና መንዝ አከባቢዎች ላይ መጠነ ሰፊ ወረራ እንደፈጸሙ የገለጠው የዞኑ አስተዳደር፣ የዞኑ ሕዝብ የሁለቱን ቡድኖች ታጣቂዎች እንዲፋለማቸው ጥሪ አድርጓል። ሕዝቡ በጦርነት ከታጣቂዎቹ የሚማርከውን ጦር መሳሪያ የግሉ እንዲያደርግ አስተዳደሩ መፍቀዱንም መግለጫው አክሎ ገልጧል።
- Category
- Ethiopian News