የኢትዮጵያ አሜሪካን ሲቪክ ካውንስል ሊቀመንበር የሆኑት ዲያቆን ዮሴፍ ተፈሪ 10 የዲያስፖራ ድርጅቶች በጋራ ለአሜሪካ ኮንግረስ አባላት የኢትዮጵያ ህገ መንግስትና የዘር ፖለቲካ አደረጃጀት በዜጎች ላይ የፈጠሩትን ኢ-ፍትሃዊነት፣ አግላይነት፣ ግፍና እልቂት ለማስረዳት በቅርቡ በተጠራው ኮንፈረስ ላይ ስለቀረቡት ጭብጦችና ተያያዥ ጉዳዮች ማብራሪያ ሰጥተውናል።
በአብይ አህመድ አመራር ተስፋ የቆረጡት የአሜሪካ መንግስት ባለስልጣናት በኢትዮጵያ በተለይ በአማራው ክልል እየተካሄደ ያለውን ጦርነትና ግጭቶች የብሄራዊ ደህንነት ስጋት [national security emergency] መሆኑን በመገንዘብ ለውጥ ለማምጣት በመሯሯጥ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
- Category
- Ethiopian News