#Ethiopia #Tigray #Welkait
The disputed #Ethiopian area of Western Tigray is expected to be a sticking point in talks aimed at ending a nearly two-year civil war. Amhara regional leaders say it must be returned to them for talks to move forward. Henry Wilkins reports from Adi Ramets.
የሰላም ንግግሩን ወደፊት ለማስኬድ ወልቃይት ወደ ትግራይ መመለስ አለበት - ሕወሓት
ምዕራብ ትግራይ ወይም ወልቃይት ተብሎ የሚጠራው አካባቢ ወደ ሁለት ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ የቆየውን የእርስ በርስ ጦርነት ለማስቆም በሚደረገው የሰላም ንግግር ወቅት አጨቃጫቂ ጉዳይ እንደሚሆን ይጠበቃል ሲል የአሜሪካ ድምፁ ሄንሪ ዊልክንስ ከአዲ-ረመፅ ባጠናቀረው ዘገባ አመልክቷል።
ከፌዴራል መንግሥቱ ጋር የወገኑ ኃይሎች አሁን ሥፍራውን እንደሚቆጣጠሩ ሪፖርቱ ጠቁሞ “የትግራይ ኃይሎች ግን የሰላም ንግግሩን ወደፊት ለማስኬድ አካባቢው ወደ ትግራይ መመለስ አለበት እያሉ ነው” ብሏል።
ሄንሪ ዊልኪንስ ባለፈው ግንቦት ለሌሎች እንደልብ የማይገኝ ፍቃድ አግኝቶ አካባቢውን ቃኝቶ ነበር። በዚህ ሪፖርት ደግሞ ሁለቱም ወገኖች አካባቢው ወዴት ይካለላል በሚለው ጉዳይ ላይ ለምን ጠንካራ አቋም እንደያዙ ይመለከታል።
- Category
- Ethiopian News