Loading...

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ስለሞት የጻፉት ግጥም ... እንጉርጉሮ ...... ሞት ማለት

Thanks! Share it with your friends!

You disliked this video. Thanks for the feedback!

Added by addis

Professor Mesfin Woldemariam’s poem about death. Issued Meskrem 1967
ሞት ማለት
ተንጋሎ መተኛት ፣አለመንቀሳቀስ ፣
ፍፁም የእንቅልፍ ዓለም ፍፁም የሕይወት ቀውስ ፣
አለመደሰት ነው ፤ ተከፍቶ አለማልቀስ ፣
የሬሳ እኩልነት ፣ እርኩስ የለ ቅዱስ ፣
በኅብረት መበስበስ ፣ በየቀኑ መፍረስ ፣
ሞት አለመስማት ነው ፤ ጆሮ ዳባ ልበስ ፣
ክርስቶስ ሲሰቀል ፣ሲፈታ በርናባስ ።
ሞት ማለት :-
አለመናገር ነው ጭው ያለ ዝምታ፣
የመቃብር ሰላም የሬሳ ጸጥታ ፣
ደሀ በሰሌኑ ሳጥን ገብቶ ጌታ ፣
የውሸት ልዩነት ተጋድሞ በተርታ ፣
አይመሽ ወይ አይነጋ ፣ጠዋት የለው ማታ ።
ሐዘን የለ ለቅሶ ፣ደስታ ፣ ፈገግታ ፣
ዘፈኑና ለቅሶው የምስጥ ሹክሹክታ ።
ሞት ማለት:-
አይረገዝበት ፣ አይወለድበት ፣
የመቃብር ዓለም ፣ጭንጋፍ ፣የጭንጋፍ ቤት
የሰው ልጅ አንደበት ትል የሚሆንበት ፣
ውሸትና እውነት በማይበርድ ፍትወት የተሳሰሩበት ፣
የድብቅብቅ ዓለም ምስጢር የበዛበት ፣
ሁሉም በየጉድጓድ የተሸሸገበት።
ሞት ማለት:-
አለመነቃነቅ ፣አለመነቃነቅ ፣
እንደ ድንጋይ መድረቅ ፣ደርቆ መወላለቅ ፣
ክብርና ውርደትን ለይቶ አለማወቅ ፣
አዘቅት ውስጥ ተኝቶ በክፋት መጥለቅለቅ ፣
በተዋኅዶ መልክ ጠላትና ወዳጅ አብሮ ሲደባለቅ ፣
ድፍርሱ ከጠራው ባሕርዩ ሲደበቅ፣
የሩቁ ሲጠጋ የቅርቡ ሲራራቅ ፣
ሞት አምሮት ሲጠፋ በልጦ ለመመረቅ።
ሞት ማለት :-
ሞት አለመስጋት ነው የግዴለሽ ዓለም ፣
ድንጋይ ተሸክሞ በውሃ ላይ መቆም ፣
ጤንነት የለበት፣ አያጠቃው ሕመም ፣
ትዝታ የለበት ፣ አይታይበት ሕልም ፣
ቡቃያው አያሸት ፣ፍሬው አይለመልም ።
ዝናብ አይዘንብበት ድርቀት ነው ዘላለም ።
ማንም አይጎዳ ማንም አይጠቀም ።
ሞት ማለት :-
አዕምሮ ፈራርሶ፣
ኅሊና በስብሶ፣
ሰውነት ረክሶ ፣
እንደግም ፣ እንደጥምብ ፣
የጭልፊቶች ምግብ ፣
የሞት ሞት ይኸ ነው ፤
ትንሳኤ የሌለወ ።
(እንጉርጉሮ -ከመስፍን ወልደማርያም ገጽ 31-32 መስከረም 1967 ዓ. ም)

Category
Ethiopian News

Post your comment