Loading...

ዶ/ር ደብረጺዮንን ጨምሮ 4 የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች “ወርቃምባ” ከተባለች ከተማ ይገኛሉ

Thanks! Share it with your friends!

You disliked this video. Thanks for the feedback!

Added by addis

ወንጀለኞችን የማደንና የመልሶ ግንባታ ምእራፍ - ዶ/ር ደብረጺዮንን ጨምሮ አራት የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ተምቤን አቢ አዲ እንዲሁም የሀውዜንና አድዋ መገንጠያ በሆነችው “ወርቃምባ” ከተባለች ከተማ ይገኛሉ

የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ጸሐዬና ጌታቸው ረዳ በአንድ ቦታ ለይ መሆናቸውን በሰሜን ዕዝ የ31 ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ሻምበል በየነ አስታወቁ፡፡ ከአራቱ ውጭ ያሉ ሌሎች አመራሮች ደግሞ አዋሳኝ በሆኑ የአማራ ክልል የተከዜ ጫፍ ስፍራዎች በዋናነትም ልዩ ስሙ “አቅመራ” በሚባል ስፍራ ሲመላለሱ መታየታቸውን ገልጸዋል፡፡- በልዩ ጥበቃ ማለትም በኮማንዶ ጭምር እተየተጠበቁ እንደሆነ የተናገሩት አዛዡ ከአራቱ ባለስልጣናት ውጭ ሌሎች ብዙም በሕዝብ የማይታወቁ ባለስልጣናት በስፍራው እንዳሉ ስለማየታቸው ተናግረዋል፡፡እነርሱን በቁጥጥር ስር የማዋሉ ስራ በአጭር ቀናት ይጠናቀቃል፡፡

 

Category
Ethiopian News

Post your comment