የሱማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሙስጠፌ ዑመር ሕወሓት የሱማሌን ህዝብ ይቅርታ እንዲጠይቅ በይፋ ተናገሩ።አቶ ሙስጠፌ ትህነግ የሱማሌን ህዝብ በጀምላ እንደ ጨፈጨፈ ይናገራሉ።በአንድ ቀን 90 ሰው ተጨፍጭፏል።50 ሰው ከእነ ነብሱ በአንድ ቀን ተቀብሯል።25 ሰው በአንድ ቀን አልቋል።የአንድ ቤተሰብ 9 ሰው በተጠራራ ፀሃይ አልቋል።ግፉ እንዳይነገር ደግሞ የሕወሓት አመራሮች እያስፈራሩ መሆናቸውን አቶ ሙስጠፌ ያክላሉ።ለዚህ ጭፍጨፋ ዋና ተዋናያኖቹ የደቡብ ምስራቅ እዝ አዛዥ የነበረው (የሞተው) ጀነራል አብርሃ ወልደማርያም (ኳርተር) አይነት የትህነግ አመራሮች መሆናቸውን ያብራራሉ።
- Category
- Ethiopian News