"የዱራሜ ከተማ መስጅድ ተቃጥሏል፣ ኢማሙም ተገድሏል" በሚል በአሉባልታ ወሬ በደቡብ ክልል ሃላባ ቁልቶ ከተማ በእስልምና እምነት ተከታዮችና በፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያን መካከል ተፈጥሮ የነበረው ግጭትና ተቃርኖ በዕርቅ ተፈታ፡፡
በሀላባ ቁልቶ በተዘጋጀ የዕርቅና የሠላም ጉባዔ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ ከመቀሳሰርና ሠላምን ከሌላ አካል ከመጠበቅ ይልቅ ዜጎች ለሠላም ዕጦት ምክንያት ከሚሆኑ ጉዳዮች ራስን በማራቅ የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ማበረከት ያስፈልጋቸዋል ብለዋል፡፡
ስምንት አባል ያለው አሸማጋይ ኮሚቴ የቀድሞ አብሮነት ለማጎልበትና ሠላም ለማስጠበቅ የመፍትኄ አቅጣጫ በማስቀመጥ ዕርቁ ዘላቂ እንዲሆን ከመንግሥት ጋር እንደሚሠሩ ተናግረዋል፡፡
በሀላባ ቁልቶ በተዘጋጀ የዕርቅና የሠላም ጉባዔ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ ከመቀሳሰርና ሠላምን ከሌላ አካል ከመጠበቅ ይልቅ ዜጎች ለሠላም ዕጦት ምክንያት ከሚሆኑ ጉዳዮች ራስን በማራቅ የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ማበረከት ያስፈልጋቸዋል ብለዋል፡፡
ስምንት አባል ያለው አሸማጋይ ኮሚቴ የቀድሞ አብሮነት ለማጎልበትና ሠላም ለማስጠበቅ የመፍትኄ አቅጣጫ በማስቀመጥ ዕርቁ ዘላቂ እንዲሆን ከመንግሥት ጋር እንደሚሠሩ ተናግረዋል፡፡
- Category
- Ethiopian News