የጎንደር ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ሥራቸውን በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸው ተሰማ፡፡
ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ ዩኒቨርስቲውን ለ13 አመታት አገልግለዋል፡፡
ይሁንና የፕሬዝዳንትነቱን ቦታ መልቀቃቸውን ለዩኒቨርስቲው ማሳወቃቸውን ሰምተናል፡፡
በዩኒቨርስቲው የአለም አቀፍና ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ተወካይ ወ/ሮ ይዳኙ ማንደፍሮ ለሸገር እንደነገሩት ዶ/ር ደሳለኝ ስልጣናቸውን ለመልቀቃቸው ዝርዝር ምክንያት አልተናገሩም፡፡
ዶ/ር ደሳለኝ በፕሬዝደንትነት ዘመናቸው የጎንደር ዩኒቨርስቲ ውጤታማ እንዲሆን አስችለውታል ተብሏል፡፡