በኦሮሚያ ክልል የሚገኘው የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የእሳት ቃጠሎ ደረሰበት፡፡
በፓርኩ የተከሰተው የእሳት አደጋ 4ኛ ቀኑን ይዟል::
የአደጋው መንስኤ በውል ባይታወቅም አደጋውን አድርሰዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
የአደጋው መንስኤም እየተጣራ እንደሚገኝ የፓርኩ የስራ ኃላፊዎች ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ገልፀዋል ።
በፓርኩ ላይ የደረሰውን አደጋ መጠን የሚያጣራ የባለሙያዎች ቡድን ወደ ስፍራው መላኩም ተገልጿል።
በአሁኑ ሰዓት የአካባቢው ፖሊስ ፣ መከላከያና ህብረተሰቡ በጋራ በመሆን ቃጠሎውን በቁጥጥር ስር ለማዋል ጥረት እያደረጉ መሆኑም ተመልክቷል፡፡