አዲስ አበባ ላይ አፈናው ቀጥሏል።

ለጊዜው ነው የምታሳቅቋቸው!

አዲስ አበባ ላይ አፈናው ቀጥሏል። ግን ለጊዜው ነው የሚያሳቅቋቸው። አማራ ክልል የነበረውን ሙቀት ገዥዎቹ ወደ አዲስ አበባ ወስደውታል። ሲያስሩ፣ ሲፍኑ በጊዜው ሊያሳቅቋቸው ይችሉ ይሆናል። ግን ቤተሰባቸው፣ ጓደኞቻቸው፣ ጎረቤታቸው፣ ከርቀት የሚያውቃቸው በሙሉ የታሰሩትን ሲያስብ የሚመጣለት የአማራ ጉዳይ ነው። የታሰሩት በአማራ ጉዳይ፣ በማንነታቸው ተጠርጥረው ነዋ።

ወገኖቻችን ያለ አግባብ ታስረው መሰቃየታቸው የሚያሳዝን ነው። ነገር ግን መታፈናቸውን ዋጋ አልባ ማድረግ የለብንም። የወገኖቻችንን መታሰር ዋጋ እንሰጠዋለን። አጀንዳ መደረግ አለበት። ፌስቡክ ላይ ብቻ አይደለም። የአዲስ አበባ ህዝብ በሚገባ አጀንዳ እንዲያደርገው ማድረግ የሚቻልባቸው መንገዶች አሉ።

የወገኖቻችን እስር ባልንፈልገውም አፈናውን በደንብ በማሳየት አዲስ አበባ ላይ መታገያ ማድረግ ይገባል። በርካታ መንገዶችም አሉ።