አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት ትኩሳት ሲሆን የታየበት አጋጣሚ በርካታ ነው፡፡ ሕገ መንግሥቱ ይህ ይጎድለዋል፣ እንዲህ ቢደረግ ወይም አንዳንድ ነገር ቢካተትበት በሚል የሚነሱ ጥያቄዎች ከባድ ተቃርኖ ሲገጥማቸው ማየት የተለመደ ነው፡፡ የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ወይም ለውጥ በተነሳ ቁጥር፣ ‹‹ሕገ መንግሥቱ የሚነካው በመቃብራችን ላይ ነው፤›› የሚል ጠንካራ አፀፋ ሲሰጥ መስማት የተለመደ ሆኖ ነው የኖረው፡፡

ከሰሞኑም ቢሆን ይህን መሰሉ አተካሮ የተደገመ ይመስላል፡፡ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ያቀረበው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጥናት መነጋገሪያ መሆኑን ተከትሎ፣ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ፓርቲ ባወጣው መግለጫ ጠንካራ ተቃውሞ ማሰማቱ የዚሁ ነፀብራቅ ሆኖ ነበር የታየው፡፡

https://www.ethiopianreporter.com/119227/

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ