በትግራይ የኤርትራ ሰራዊት መንገድ በመዝጋቱ እርዳታ እየደረሰ አይደለም ተባለ

በትግራይ ክልል ሰሜናዊ ድንበር አንዳንድ አካባቢዎች፣ በተለይም ለኢሮብ ወረዳ ሕዝብ፣ ዛሬም ሰብዓዊ ርዳታ እየደረሰ እንዳልኾነ፣ አንድ የአካባቢው ተወላጅ ለቪኦኤ ገለጹ፡፡ የዚኽም ምክንያት፣ ወደ ወረዳው የሚገባው መንገድ በመዘጋቱ እና በየትኛውም ወገን ትኩረት በመነፈጉ እንደኾነ አስረድተዋል፡፡

የትግራይ ክልል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በበኩሉ፣ መንገዱን የኤርትራ ሠራዊት ኬላ ስለዘረጋበት የሰብአዊ ርዳታ ለማቅረብ እንደተቸገረ አስታወቀ፡፡

የኤርትራ መንግሥት፣ ከዚኽ ቀደም የሚቀርብበትን የትኛውንም ክሥ አልተቀበለም። የኢሮብ ወረዳን ሕዝብ በተመለከተም፣ እስከ አሁን የሰጠው ምላሽ የለም።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ዘገባ ያገኛሉ።