ብልፅግና እና ሕወሓት በአደራዳሪዎች ጉዳይ ለመግባባት አልቻሉም ተባለ ።

የብልፅግና መንግሥት ከህወሓት ጋር የሚደረግ የሰላም ድርድር “በአፍሪካ ኅብረት ሸምጋይነት መካሄድ አለበት” የሚለውን አቋሙን በዚህ ሳምንት በድጋሚ ቢያስታውቅም ትግራይ ክልልን እያስተዳደረ ያለው ህወሓት በበኩሉ በአፍሪካ ኅብረት ላይ እምነት እንደሌለው ገልፆ ድርድሩ “በኬንያ ሸምጋይነት ይካሄድ” በሚለው አቋሙ እንደፀና ነው።

የሰላም ንግግር ተስፋና ሁለቱ ወገኖች አሁን የገቡበትን አጣብቂኝ በተመለከተ የቪኦኤው ሪፖርተር ሄንሪ ዊልክንስ አዲስ አበባ ላይ ተንታኞችንና ፖለቲከኞችን አነግሯል።

ሙሉውን ከተያያዘው ዘገባ ያዳምጡ።