ዋና ተቋራጮች ንዑስ ተቋራጮችን እንዲያሳትፉ የሚያስገድድ መመርያ ሊዘጋጅ ነው

ዋና ተቋራጮች ንዑስ ተቋራጮችን እንዲያሳትፉ የሚያስገድድ መመርያ ሊዘጋጅ ነው

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ የአገር ውስጥም ሆኑ የውጭ ሥራ ተቋራጮች፣ በሥራቸው ንዑስ ሥራ ተቋራጮችን እንዲያሳትፉ ለማድረግ የሚያስችል መመርያ ወይም የአሠራር ሥርዓት ለመዘርጋት ጥናት እየተደረገ መሆኑን፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት አስታወቀ።