በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተነስቶ በነበረው ብጥብጥ በጥይት የተመታው ተማሪ ሕይወቱ አለፈ

በትናንትናው እለት በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተነስቶ በነበረው ብጥብጥ ወቅት ከኦሮምያ ልዩ ሀይል በተተኮሰ ጥይት ከተመቱት ተማሪዎች መሀከል የ4ኛ አመት የሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ተማሪ የነበረው ደቻሳ ቦጋለ ዛሬ ከሰአት ህይወቱ ማለፉን ጓደኞቹ በስልክ ነግረውናል።

በአጠቃላይ 12 ተማሪዎች በትናንቱ ብጥብጥ ወቅት በጥይት እንደተመቱ የታወቀ ሲሆን ደቻሳ የመጀመርያው ህይወቱን ያጣ ተማሪ ሆኗል።

Ethio News flash Exclusive News