የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት ወደ ጎጃም አካባቢዎች በገፍ እየተጓጓዘ ነው

ፎቶ ፋይል

በርካታ የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት ወደ ባህር ዳርና ጎጃም አካባቢ እየተጓጓዘ እንደሆነ መረጃ ደርሶናል። ምናልባትም በጎጃም ተጨማሪ ጥፋት ለመስራት ታስቦ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አለ።

ዶር ሰማ ጥሩነህ የክልል ርዕሰ መስተዳድር ለመሆን ካለው ስግብግብ ፍላጎት ከአብይና ከኦህዴድ ትዕዛዝ በመቀበል የአማራን ምድር የጦርነት ቀጠና እያደረገው እንደሆነ ተጨባጭ መረጃ ደርሶናል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶር ይልቃል ከፋለ የመወሰን አቅም እንደለለውና በተለይም የመከላከያ ትዕዛዝ በም/ርዕሰ መስተዳድሩ ዶር ሰማ ጥሩነህ እየተመራ እንደሆነ ተጨባጭ መረጃ ደርሶናል።

መራዊ፣ ዳንግላ፣ እንጅባራ፣ ፍኖተ ሰላም፣ ማርቆስ ቀጥይ ከአርሶ አደር እስከ ፋኖ፣ የአብን አባላት፣ የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች አፈና የሚፈፀምባቸው አካባቢዎች እንደሆኑ ታውቋል።