ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ሰላም ማውረዳቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ ሁለቱን ሀገራት የሚያገናኙ መንገዶችን እና ድንበሮችን መክፈታቸው ይታወሳል። ሆኖም በሁመራ አካባቢ ያለው ድንበር እስካሁን አለመከፈቱ በነዋሪዎች ዘንድ ቅሬታ ፈጥሯል፡፡
በኢትዮጵያ በኩል ያሉ የአካባቢው የመንግስት ባለስልጣናት በበኩላቸው ድንበሩ ያልተከፈተው የኤርትራ መንግስት ባለመፈቀዱ ነው ይላሉ፡፡ ውይይት ተደርጎ የድንበር መንገዱ በቅርቡ ይከፈታል ብለው እንደሚጠብቁም ይናገራሉ፡፡
ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ሰላም ማውረዳቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ ሁለቱን ሀገራት የሚያገናኙ መንገዶችን እና ድንበሮችን መክፈታቸው ይታወሳል። ሆኖም በሁመራ አካባቢ ያለው ድንበር እስካሁን አለመከፈቱ በነዋሪዎች ዘንድ ቅሬታ ፈጥሯል፡፡
በኢትዮጵያ በኩል ያሉ የአካባቢው የመንግስት ባለስልጣናት በበኩላቸው ድንበሩ ያልተከፈተው የኤርትራ መንግስት ባለመፈቀዱ ነው ይላሉ፡፡ ውይይት ተደርጎ የድንበር መንገዱ በቅርቡ ይከፈታል ብለው እንደሚጠብቁም ይናገራሉ፡፡
የትግራይ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል በበኩላቸው ድንበሩ እንዲከፈት ከመጀመርያው ጀምሮ ፍላጎት እንደነበር በመግለፅ እየተደረገ ባለው ንግግር በቀጣይነት ይከፈታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል፡፡
በሑመራ ኦምሓጀር በኩል ያለው የኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር በተከዘ ወንዝ የሚለያይ ሲሆን፣ ቀደም ብሎ የተሰራ ድልድይ ሁለቱን ሀገራት ያገናኛል፡፡