ለውጭ ኩባንያ የተሸጠው ኤድና ሞል ታድሶ ሲጠናቀቅ ይከራያል መባሉ  ግርታ ፈጥሯል

ባለፈው ዓመት ሚያዝያ ወር 2013 ዓ.ም. ላይ በተደረገው ጨረታ፣ ቦሌ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አካባቢ የሚገኘውን ኤድናሞል ሕንፃ በ810 ሚሊዮን ብር የገዛው የቻይናው ኩባንያ ኢስት ስቲል፣ ሕንፃውን አድሶ ለገበያ ማዕከልነት እንደሚያከራይ መግለጹ ከኢንቨስትመንት ሕጉ ጋር በተያያዘ ይቻላል ወይስ አይቻልም የሚለው ግርታ ፈጥሯል፡፡