ኤርትራ ተቃራኒ ሃሳብ ያላቸው ዜጎች እስር ቤት የሚወረወሩባት አገር ሆና መቀጠሏ እንደሚያሳስባት አሜሪካ ገልጻለች።

አሜሪካ ኤርትራ ከ25 ዓመት በፊት ያረቀቀችውን ሕገ መንግሥቷን ተግባራዊ እንድታደርግ፣ ነጻ ምርጫ እንድታካሂድ እና ዜጎች ሃሳባቸውን በነጻነት እንዲገልጡ እንድትፈቅድ አሥመራ በሚገኘው ኢምባሲዋ በኩል ጠይቃለች።

ኤርትራ ተቃራኒ ሃሳብ ያላቸው ዜጎች እስር ቤት የሚወረወሩባት አገር ሆና መቀጠሏ እንደሚያሳስባት አሜሪካ ገልጻለች። የአሜሪካ ኢምባሲ ይህን ያለው፣ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገ/መስቀል የአሜሪካ የምርጫ ሥርዓት በገንዘብ የሚዘወር መሆኑን በትዊተር ገጻቸው ላሰፈሩት ስላቃዊ ትችት ምላሽ ነው።

May be an image of 1 person and text that says 'Yemane G. Meskel @hawelti Mar 21 If this account is fully accurate, it can only provoke much more profound issues: the inherent pitfalls of distortion when & if components of foreign policy are auctioned to lobbyists on a highest bidder basis and/or political campaign contributors'

ሆኖም የማነ የሰጡት አስተያየት እውነታነት እንዳለው ኢምባሲው ገልጦ፣ ጉዳዩን አሜሪካዊያን በነጻነት እየተወያዩበት እንደሆነ አውስቷል።