በጋምቤላ ከደቡብ ሱዳን ድንበር አቅራቢያ በተከሰተ የጸጥታ ችግር ሰዎች ተፈናቀሉ

በደቡብ ሱዳን የሚንቀሳቀስ ታጣቂ ቡድን ወደ ጋምቤላ ክልል ዘልቆ በመግባት የአንድ ሰው ሕይወት ማጥፋቱን እና በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ማፈናቀሉ ተገለጸ።