መንግስት ኢኮኖሚውን ለማሻሻል እና የግሉ ሴክተርን ሚና ለማስፋት በያዘው እቅድ መሰረት የአዲስ አበባ ጅቡቲ የባቡር መስመርን ወደ ግል ለማዛወር ከአውሮፓ ኩባንያዎች ጋር እየተነጋገረ ነው።
–
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው የባቡር መስመሩ ሙሉ በሙሉ ወደ አገልግሎት እንዲገባና ቀልጣፋ ለማድረግ ተጨማሪ 800 ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት ያስፈልገዋል።
–
የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን በከፊልም ሆነ በሙሉ ወደ ግል ለማዘዋወር ከታቀዱ ዋና ዋና የመንግስት ኢንተርፕራይዞች አንዱ ነው። የፕራይቬታይዜሽን ሒደቱን በተመለከተ ዝርዝር መረጃ ገና ይፋ አልሆነም።
–
በኮርፖሬሽኑ ተቀጥሮ የባቡር ሀዲዱን የሚያስተዳድረውን የቻይና ኩባንያዎች የተወሰነ ድርሻ እንዲኖራቸው ብንጠይቅም ፍቃደኛ አልሆኑም ያሉት የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ጥላሁን ሳርካ 4 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወጪ ወቶበት የተገነባው የባቡር ሀዲድ የኢንቨስትመንት ወጪው ብዙ በመሆኑ ያንን ያህል ገንዘብ የሚያወጣ ካምፓኒ ማግኘት አስቸጋሪ ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ።
–
የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ እንዳሉት መንግስት የባቡር መሰረተ ልማቶችን ለማሻሻል ካቀዳቸው እቅዶች መካከል የግሉ ዘርፍ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገባ ማድረግ አንዱ ነው ።