የህወሓት ተዋጊዎች በአማራ ክልል ፈጽመውታል የተባለው ግድያ እንዲመረመርና ተጠያቂነት እንዲሰፍን አሜሪካ ጠየቀች

የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቷ አስገድዶ መድፈርን ያካትታል የተባለለትን ግድያ በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል

ዋሽንግተን ተዋጊዎቹ በክልሉ ተፈጽሟል በተባለው ግድያ እጅግ ማሰቧን አስታውቃለች

የህወሓት ተዋጊዎች በአማራ ክልል ፈጽመውታል የተባለው ግድያ እጅግ እንዳሳሰባት አሜሪካ አስታወቀች፡፡

ዋሽንግተን በወርሃ ነሃሴ መጨረሻ እና በመስከረም መባቻ ግድም እንደተፈጸሙ በአምነስቲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት በተደረጉ ጥፋቶች ማሰቧን አስታውቃለች፡፡

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስገድዶ መድፈርን ያካትታል የተባለለትን ግድያ በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል፡፡

The United States is gravely concerned by the reports of atrocities, including sexual violence, committed by fighters affiliated with the Tigray People’s Liberation Front in the Amhara region of Ethiopia in late August and early September 2021, as described in a recent Amnesty International report. We call on all armed actors to renounce and end all human rights abuses and violence against civilians. It remains our firm position that there must be credible investigations into and accountability for atrocities as part of any lasting solution to the crisis.

Continued reports of atrocities underscore the urgency of ending the ongoing military conflict. We continue to engage parties to the conflict to urge a halt to the violence, an end to atrocities, the unhindered provision of life-saving humanitarian assistance, and a peaceful resolution to the conflict.

በመግለጫው ሁሉም የውጊያው ተዋናዮች በሰላማዊ ዜጎች ላይ በማድረስ ላይ ያሉትን የሰብዓዊ መብቶች ረገጣ እና ጥቃት እንዲያቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡

ለችግሩ ዘላቂ እልባት መስጠት ይቻል ዘንድ ለተፈጸመው ግፍ ታማኝነት ያለው ምርመራ ተደርጎ ተጠያቂነት ሊኖር ይገባል የሚለው ጽኑ አቋም እንዳለውም አስታውቋል ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ በመግለጫው።

ግድያዎች መቀጠላቸውን የሚያመለክቱ ሪፖርቶች አሁንም መውጣት መቀጠላቸው ለግጭቱ በፍጥነት ማብቂያ ሊበጅለት እንደሚገባ የሚያሳይ ነው ሲልም ገልጿል፡፡

መስሪያ ቤቱ ግጭቱንና ግድያዎችን በማስቆም ሰብዓዊ እርዳታዎችን በተሟላ ሁኔታ ለማድረስና ሰላማዊ የመፍትሔ መንግዶችን ለማፈላለግ ከግጭቱ ተዋናዮች ጋር ተቀራርቦ መስራቱን እንደሚቀጥልም አስታውቋል፡፡

አምነስቲ ከሳምንት በፊት ባወጣው የምርመራ ሪፖርት “ህወሓት፤ በአማራ ክልል የጦር ወንጀል መፈጸሙን የሚሳዩ ማስረጃዎች እየጨመሩ ነው” ሲል ማስታወቁ የሚታወስ ነው፡፡

በቆቦ እና በጭና አካባቢዎች የተፈጸመ ነው ባለው በዚህ ወንጀል የህወሓት ታጣቂዎች በርካቶችን መግደላቸውን እና የ14 ዓመት ታዳጊዎችን ጨምሮ በርካታ ሴቶችን መደፈራቸውን አምነስቲ መግለጹም አይዘነጋም፡፡

አል-ዐይን