ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ መግለጫ አወጡ

ኢትዮጵያ፣ ግብፅና ሱዳን ለህዝባቸው ሰላም፣ ትብብር፣ አብሮ መኖርና ልማት ሊሰሩ የሚገባቸው ጊዜ አሁን መሆኑን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ባወጡት መግለጫ፥ ግድቡ ለሀገራቱ ህዝቦች ሰላማዊነት፣ ትብብር፣ አብሮ መኖርና የመልማት እድልን ይዞ የመጣ መሆኑን አስታውቀዋል።
የናይል ወንዝ በአጠቃላይ፤ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት በተለይ ለሶስቱ ሀገራት የሰላም፣ የትብብርና የልማት ዓላማ መሳካት ወሳኝ መሆኑንም አመልክተዋል።
Image

Image